Sunday, May 5, 2013

“አንድነት” የዜጐች መፈናቀልን የማስቆም እንቅስቃሴ ሊጀምር ነው

“አንድነት” የዜጐች መፈናቀልን የማስቆም እንቅስቃሴ ሊጀምር ነው

አገር አቀፍ ምሁራን የሚሣተፉበት የፓናል ውይይትም ያካሂዳል አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ /አንድነት/ የዜጐችን መፈናቀል ለማስቆምና በዜጐች መፈናቀልና እንግልት ላይ ተሣታፊ የሆኑ የመንግስት ሀላፊዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ የሚያግዝ ፒቲሽን ለማስፈረም እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ፡፡ ኢትዮጵያዊ ምሁራን የሚሣተፉበትና መፈናቀሉ እያስከተለ ባለው ጉዳት ዙሪያ በመወያየት የመፍትሄ ሀሣብ የሚመነጭበት አገር አቀፍ የፓናል ውይይት እንደሚካሄድም ፓርቲው ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡
የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሀላፊና የኤዲቶሪያል የቦርድ አባል አቶ ዳንኤል ተፈራ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ አንድነት እየተካሄደ ያለው ዜጐችን የማፈናቀል ተግባር አገር አቀፍ ይዘት ያለው መሆኑን ያምናል፡፡ ይህን አገር አቀፍ ማፈናቀልና እንግልት ለአንዴና ለመጨረሻ ለማስቆም ፓርቲው ፒቲሺን ለማሠባሠብ መዘጋጀቱን የገለፁት አቶ ዳንኤል፤ ይህን ተግባር ለማከናወን በፓርቲው የፖለቲካ ጉዳይ የበላይ መሪነት አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ መዋቀሩንም ጨምረው ገልፀዋል፡፡ “የኮሚቴው አባላት የተዋቀሩት ከፖለቲካ ጉዳይ፣ ከህዝብ ግንኙነት፣ ከማህበራዊ ጉዳይ እና ከፓርቲው ሁለት አባላት ተጨምረው ነው” ያሉት ሀላፊው፤ ህዝቡ እና ይህ ህገ-ወጥ ተግባር እንዲቆም የሚፈልግ የትኛውም አካል ፊርማውን በማኖር ተቃውሞውን እንዲገልፅ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
የፊርማ ማሠባሠቡ ሥራ በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ እንደሚከናወን የገለፁት አቶ ዳንኤል፤ ከዚያ በኋላ ፓርቲው ከህግ ክፍሉ ጋር በመመካከር ጉዳዩን ለሀገር ውስጥም ሆነ ለዓለም ፍ/ቤቶች እንደሚያቀርቡት ተናግረዋል፡፡ አገር አቀፉን የፓናል ውይይት አስመልክተው አቶ ዳንኤል ሲናገሩ፤ ውይይቱ በዋናነት የሚያተኩረው ዘርን መሠረት አድርገው የሚፈፀሙ መፈናቀሎች የኢትዮጵያን ህዝብ አንድነትና ሠላም የሚያፈራርስ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያዊ ምሁራን በውይይቱ በመሣተፍ፣ የመፍትሄ ሀሣብ በማምጣትና ህዝቡን በማስተማር ዜጐችን የመታደግ ሀላፊነት አለባቸው ብለዋል - አቶ ዳንኤል፡፡ “የመፈናቀል ጉዳይ አገር አቀፋዊ እየሆነ በመምጣቱ አስጊነቱን በማጉላት እና እልባት በማበጀት አስፈላጊነት ላይ አንድነት ጠንካራ እምነት አለው” ያሉት አቶ ዳንኤል፤ ለፊርማ ማሠባሠቡም ሆነ ለፓናል ውይይቱ ፓርቲያቸው እንቅስቃሴ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡
ውይይቱ መቼ እና የት እንደሚካሄድ የተጠየቁት ሀላፊው፤ ውይይቱ አገር አቀፍ በመሆኑ ሠፊ አዳራሽ እንደሚያስፈልግ ገልፀው ቦታው ለጊዜው አለመወሠኑን፣ ነገር ግን በአንድነት ፅ/ቤት አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ መቼ ይካሄዳል ለሚለው ጥያቄም በአንድ ወር እና ከዚያ ባነሠ ጊዜ ውስጥ እንደሚካሄድ ገልፀዋል፡፡ “ማፈናቀል ማስቆም የሚቻለው ህዝቡ የችግሩ ሠለባ እንዳይሆን በማንቃትና በማስተማር ብቻ ነው፤ አገራዊ ችግርን የሚፈታው ደግሞ ህዝብና ህዝብ ብቻ ነው” ያሉት አቶ ዳንኤል ለዚህም ምሁራን ባላቸው ተሠሚነትና በሚያፈልቁት ሀሣብ ህዝቡን ማንቃት፣ አገራዊ ፋይዳ ያላቸው በመሆኑ ከፓናል ውይይቱ ትልቅ ለውጥ እንደሚጠብቁም ተናግረዋል፡፡ እስከ ዛሬ በደረሱት መፈናቅሎች ብዙ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ልቦናዊ ቀውሶች መፈጠራቸውን የገለፁት የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ፤ በቅርቡ ከቤኒሻንጉል የተፈናቀሉት ወገኖችን ጉዳይ በስፍራው ተገኝቶ የሚያጠና ልኡክ በመላክ ፓርቲው መረጃ ማሠባሠቡን እና ይህንንም ተጨባጭ ማስረጃ ለፒቲሽን ማሠባሠቡና ለፓናል ውይይቱ መነሻ እንደሆናቸው አቶ ዳንኤል ተናግረዋል፡፡ ይህን ድርጊት የሚያወግዝና የሚቃወም የትኛውም ድርጅትና ግለሠብ ፊርማውን በማኖር እና ምሁራንም በውይይቱ በመሣተፍ ከፓርቲው ጐን እንዲቆሙ ትብብር ጠይቀዋል፡፡

አርቲስት ቻቺ ታደሠ ለአፍሪካ ህብረት በግል ኮንሰርት አዘጋጀች

የአፍሪካ ህብረት የተመሠረበትን 50ኛ አመት ምክንያት በማድረግ በቻቺ ኢንተርናሽል አርቲስት ማናጅመንት የተሰናዳ የአፍሪካ ሙዚቃ ፌስቲቫል ግንቦት 3 እና 4 በሚሊኒየም አዳራሽ ይቀርባል፡፡ በአርቲስት ቻቺ ታደሠ በሚመራው ዝግጅት ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰባት የአፍሪካ ሃገራት የተውጣጡ ሙዚቀኞች ተሳታፊ እንደሚሆኑ አዘጋጆቹ በጋዜጣዊ መግለጫቸው አስታውቀዋል፡፡ አርቲስት ቻቺ ታደሰ፤ ዝግጅቱን እንዲያደምቁ የ40 አገራት አርቲስቶችን ለመጋበዝ ብትሞክርም በኤምባሲዎች ትብብር የተሳካው የስድስት ሀገራት መሆኑንና ሂደቱ አድካሚ እንደነበር አመልክታለች፡፡
በዝግጅቱ ላይ ከኢትዮጵያ ሃይሌ ሩትስ እና ቺጌ ባንድ እንዲሁም ቻቺ ራሷ “I am an African” የሚለውን ዘፈኗን በመዝፈን ተሣታፊ እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚካሄደውን የሙዚቃ ዝግጅት ፌስቲቫል ለመታደም ከጠዋቱ 3-12 ሰዓት ለሚቀርበው ለአዋቂዎች 50 ብር፣ ለህፃናት በነፃ ሲሆን ለምሽት የሙዚቃ ዝግጅቶች ለአንድ ሰው መግቢያ የ200 ብር ቲኬት መዘጋጀቱን አስተባባሪዎቹ አስታውቀዋል፡፡
Read 124 times

Saturday, May 4, 2013

ጆሲ አዲስ ቶክ ሾው ሊጀምር ነው

ጆሲ አዲስ ቶክ ሾው ሊጀምር ነው

    
ድምፃዊ ዮሴፍ ገብሬ (ጆሲ) አዲስ የቴሌቪዥን ቶክ ሾው ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ፡፡ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (EBS) የሚጀመረው የቴሌቪዥን ቶክ ሾው Jossy in z House የሚል ርእስ ያለው ሲሆን ዝግጅቱ በፋሽን እና ስነጥበብ ላይ ያተኩራል፡፡ የነገ ሳምንት በእለተ ትንሳኤ የሚጀመረው ዝግጅት ዘወትር እሁድ ምሽት ከሁለት ሰዓት ጀምሮ ለአንድ ሰዓት የሚታይ ሲሆን ሐሙስ ከምሽቱ 4 ሰዓት ይደገማል፡፡

የ“ፖለቲካዊ ፍልስፍና” መጽሃፍ ለዛና ቁምነገር

!

Written by  ደረጀ በላይነህ
 
 
 
ሰሞኑን እጄ ገብቶ ያነበብኩት መጽሃፍ “ፖለቲካዊ ፍልስፍና” የሚል ርዕስ ያለው ሲሆን የ“ኢቦኒ” መጽሄት ዋና አዘጋጅ በሆነው በቃል ኪዳን ይበልጣል የተዘጋጀ ነው፡፡ መጽሃፉ በዓለማችን የታወቁ ታላላቅ ፈላስፎችን ታሪክና ስራ የያዘ ሲሆን ፍልስፍና ምንድነው? ፍልስፍና ለምን? የፍልስፍና ታሪክ፣ ዐበይት የፍልስፍና ክፍሎች፣ ሌሎች የፍልስፍና ዘርፎች፣ ነገረ ፖለቲካዊ ፍልስፍና…ወዘተ በሚሉ ክፍሎች ተከፋፍሏል፡፡ ዐበይት የፍልስፍና ክፍሎች በሚለው ርዕስ ስር ዲበአአካል፣ሥነ ዕውቀት፣ሥነ ምግባር፣ሥነ ውበት፣ሥነ አመክንዮ እያለ አስቀምጧቸዋል፡፡ ከአምስቱ በተጨማሪ ራሳቸውን የቻሉ ናቸው ተብሎ እንደ ቅርንጫፍ የሚታዩትን የአዕምሮ ፍልስፍና፣የቋንቋ ፍልስፍና፣የትምህርት ፍልስፍና፣የሃይማኖት ፍልስፍና በሚል ዘርዝሯቸዋል፡ መጽሃፉ ከጉዳዮች ቅደም ተከተልና የጽሁፉ ፍሰት ጀምሮ እጅግ ደስ የሚያሰኝ፣ማራኪና ዕውቀት ሰጪ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡ የብዙ ጸሃፊዎች ችግር ስለጉዳዩ ዕውቀት እያላቸው እንዴት አድርገው እንደሚጽፉ ያለማወቃቸው ነው፡፡ እኔ ደግሞ ጥሎብኝ ውበት አደንቃለሁ፡፡ ፍሬነገሩ ብቻ አይማርከኝም፡፡
ውበት መፍጠርም ውድ ተሰጥዖ ነው፡፡ የተመኘ ሁሉ አያገኘውም፡፡ መጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ እንኳ ነቢዩ ኢሳያስ በዘይቤ ያበዱ ቅኔዎችን ሲጽፍ፣ ሁሉም ያንን አላደረጉትም፡፡ ሉቃስ ወንጌሉን በምሳሌያዊ ንግግሮች ሲያጅብ፣ ሌሎቹ ያን ያህል አላስጌጡትም፡፡ የቃል ኪዳን “ፖለቲካዊ ፍልስፍና” ከጠበቅሁት በላይ ስለነበር ታክሲ ውስጥ ሆኜ ነው ያገባደድኩት፡፡ መጽሃፉ ውስጥ ምናልባት የምናውቃቸው ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ፤ይሁንና የማናውቃቸውን አዳዲስ ነገሮች ይጨምርልናል፡፡ የጥንቱን ፈላስፎች እነ አፍላጦንን፣ አርስጣጣሊስን ጨምሮ ኒኮሎ ማኪያቬሌን፣ጆን ሎክን፣ኤድመንድ በርክን፣ ዣን ዣክ ሩሶን ወዘተ ትውልዳቸውን፣ ዕድገትና ፖለቲካዊ አመለካከታቸውን ያሳየናል፡፡ ሌላው ትልቁና ጥሩው ነገር ጸሃፊው ሰበካ ውስጥ ሳይገባ ሃሳቡን ለአንባቢ መተው ነው፡፡ አንብቦ ይህ ጥሩ ነው- ይህ መጥፎ ነው የሚል እድል ለአንባቢው ትቷል፡፡ ለምሳሌ ብዙ ጊዜ ብዙዎቻችን በማኪያቬሌ ሃሳብ በጣም እንበሳጫለን፤እንራገማለን፡፡
ምናልባትም ሊከብደን ይችላል፡፡ በተለይ እዚህ መጽሃፍ ውስጥ ያልተካተተውና እንግሊዝኛው መግቢያ ላይ ያለው ስለ (inspiration)ወይም በአማርኛ የነገረ መለኮት ምሁራን እንደሚሉት “አፊዎት” የሚናገረው ነገር በጣም ያስጠላል፡፡ ጸሃፊው ይህንን ያለመጥቀሱን አድንቄያለሁ፡፡ ምክንያቱም አንባቢውን ይገፋልና! ከማኪያቬሌ ሃሳቦች ውስጥ ጥቂት ላንሳ መሰለኝ፡፡ እንዲህ ይላል፡- “የሰዎች ባህርያት በተለያዩ ስሜቶች ሊቀረጹ ይችላሉ፡፡ ኑሮ የተመቻቸውም ያልተመቻቸውም አዲስ ነገር ይፈልጋሉ፡፡ የለውጥ ፍቅር የትም ቦታ ለሚከሰት ፈጠራ መለኮሻው ነው፤ ስለዚህ ሰው በብዙሃን እይታ አዲስ ወይንም እንግዳ መስሎ ከታየ ሃሳቡ እርባና ያለውም የሌለውም ቢሆን በስኬት መሰላል ወደ ላይ መመንጠቁ ይገመታል፡፡ሌሎች ብርቱ ስሜቶቻችን ድርጊቶቻችንን ይወስናሉ፡፡ ፍቅርና ፍርሃት፡፡ ሰዎች እንዲፈሩት የሚያደርግ ፤ሰዎች እንዲወዱት የሚያደርገውን ያህል ተጽእኖ መፍጠር ይችላል፡፡ ቶማስ ጀፈርሰን እንዲህ ቢልም “…and not to blast the confidence we have inspired of proof that a government of reason is better than one of force.” ጥልቅ ምኞትም በማንነታችን ላይ ከፍተኛ ጉልበት አለው፡፡
ሰዎች የቱንም ያህል ቢያድጉ ከቁመታቸው የሚልቅ ምኞት በልባቸው ውስጥ ይኮተኩታሉ፡፡ የምኞት ሃይል የተመኘነውን ስናገኝ ከሚሰማን እርካታ ይበልጣል፡፡ ስለዚህ ምኞት ተጨማሪ እየጠየቀ ዘወትር ከጉያችን አይጠፋም፡፡ ሰዎች የነጻነት ፍላጎትም ኣላቸው፡፡ ነጻ ሆነው በማንም ሳይገደቡ ህይወታቸውን እንዲመሩ፣ዝንባሌያቸውን እንዲከተሉ፤ጥሩ ነው የሚሉትን እንዲያባርሩ ይሻሉ፡፡ ነጻ መሆን (በሌሎች እስር ወይም ጥገኝነት ስር ላለመዋል)ያለው እርግጠኛ መንገድ ሌሎችን ጥገኛ ማድረግ ላይ የተመሰረተ ስለሆነ ሰው የበላይ መሆንን ያፈቅራል፡፡ እንደ ማኪያቬሌ እምነት በዚህ ፍላጎት መነሻነት በህዝብና መንግስት መካከል ፍልሚያ ሊኖር ግድ ነው፡፡ የማኪያቬሌ ሳይንስ ደግሞ ፖለቲካል ሳይንስ ነው- በቅርቡ እንደሚጠራበት ስያሜ፡፡ ምክንያም ፖለቲካል ሳይንስ የሚያጠናው፤ መንግስት በህብረተሰቡ ውስጥ ያለውን ተግባር ነውና!...የፖለቲክስ ኤንድ ሶሳይቲ ጸሃፊ ሚካኤል ሩሽ እንደሚሉት “political science is therefore the study of the function of the government in society. ማኪያቬሌ ፖለቲካዊ ስልጣን በህዝብ ፈቃደኝነት ላይ የሚመሰረት ነው ይላል፡፡ በዚህ ሃሳብ ደግሞ አብርሃም ሊንከን፣ ቶማስ ጀፈርሰንና ሌሎችም የአውሮፓና የአሜሪካ ፖለቲከኞች ይስማማሉ፡፡ ይሁንና ማኪያቬሌ ይህንን ፍቃደኝነቱን እንደ ህጻን አባብሎ ከህዝብ ጉያ መንጠቅ ይቻላል ብሎ ያምናል፡፡
እንዲህ፡-ህዝብ ክብሩ፤ንብረቱ እና ደህንነቱ ከተጠበቀለት ስለ ፖለቲካዊ ፖሊሲዎች ፤ስለመንግስት ስርዓቶች እና ቅርጾች ጠልቆ በመመራመር ራሱን አያደክምም፡፡ ደስ እያለው ፈቃዱን ይቸራል፡፡….እያለ ይቀጥላል፡፡ ይህንን መርህ ደግሞ ብዙ የአፍሪካ መሪዎች እንደሚጠቀሙበት አይተናል፡፡ የኛም ሃገር መሪዎች ከምንወዳቸው ይልቅ እንድንፈራቸው ስላደረጉን፣ ስናማቸው እንኳ ግራና ቀኝ ተገላምጠን ነው፡፡ ካለበለዚያ መታወቂያና ሽጉጥ አውጥቶ “የህዝብ ደህንነት ነኝ” ቢል የማን ያለህ ይባላል፡፡ አያድርስ እንጂ!...እግዜር የምንፈራው ሳይሆን የምንወድደውን መሪ ይስጠን! እኔ ተቃዋሚዎቹም ከዚህ የተለዩ ናቸው ብዬ አላምንም፡፡ የተከበብነው በጉልበተኞች ነው፡፡ ከራሱ ሃሳብ በስተቀር የሌላውን የተለየ ሃሳብ የማያስተናግድ ፕሬስም አምባገነን ነው፡፡ ጠመንጃ ከያዘማ…አለቀልን፡፡ አምባገነንነት የሚጀምረው ከዚህ ነው፡፡ ምናልባት እነዚህ ሰዎች ስልጣን ቢይዙ የዛሬውን ያህል እየታሰሩም መጻፍ የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ሁላችንም ውስጥ አምባገነንነት አብሮ ሳያድግ አልቀረም፡፡ ማኪያቬሌ የሚለውን አንድ ሃሳብ ልበል መሰለኝ - ባልደግፈውም፡-“ሁለት አይነት የፍልሚያ ስልቶች እንዳሉ ማወቅ አለባችሁ፡፡አንደኛው በህግ ሌላኛው በሃይል፡፡ የመጀመሪያው ዘዴ የሰዎች ነው፤ሁለተኛው የአራዊት፡፡ ግን ቀዳሚው መንገድ ሁልጊዜም በቂ ስለማይሆን ሁለተኛውን መተግበር የግድ ይሆናል፡፡
ቀጣዩ ቶማስ ሆብስ ነው፡፡ ይህ ሰው የዴሞክራሲን አስተሳሰብ የሚያጣጥልና ባላባታዊውን አገዛዝ የሚደግፍ እንደሆነ መጽሃፉ ያሳያል፡፡ ሆብስ ስለ ሳቅ የሚለው ነገር ትንሽ ለየት ይላል፡፡ “ሳቅም ሆነ ጨዋታ አንድም በኣንዳች ዘርፍ የበላይነት በማግኘት ለራስ የሚሰጥ ዕውቅና እና ሙገሳ ነው፡፡ ወይንም በሌሎች ላይ እንከን ውድቀትን ማየት የሚፈጥረው የደስታ ስሜት ነው፡፡ ሆብስ ስለ ሰዎች ልዩነት የሚናገረው ቀለል አድርጎ ነው፡፡ ለምሳሌ እንዲህ ይላል፡-“ተፈጥሮ ሰዎችን በአዕምሮና በአካል ዘርፎች እኩል አድርጋ ነው የሰራቻቸው፡፡ ምንም እንኳን ለሌሎቹ በአካል ገዝፎ የሚታይ ወይንም በአእምሮ ደከም ብሎ የሚስተዋል ባይጠፋም፤በጥቅሉ ሲመረመር በሰውና በሰው መካከል ያለው ልዩነት እምብዛም ነው፡፡ የሚበልጥ የመሰለው ሰው ብልጫው ከሌሎች የተሻለ ዕድል ተጠቃሚ የማያደርገው ነው፡፡ ሆብስ እንዲህ ይላል የሰውን ልጅ አስመልክቶ፡፡…ሰው በአንድ ወቅት ይኖር የነበረው ያለ መንግስት ነው፡፡ ምክንያቱም ተፈጥሯዊው የአኗኗር ሁኔታ ያ ነው፤ ነገር ግን ይህ “ተፈጥሯዊ የነገሮች ሁኔታ”ወይ ሊከሰት የማይቻል ወይንም የማይመች ሆኖ ተገኝቷል፡፡
ስለሆነም በተወሰነ ወቅት ላይ የተፈጥሯዊው ሁኔታ ኗሪዎች ተሰባሰቡና በንቁ ልቦናቸው ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተቋማትን ለመመስረት ተስማሙ-- ይልና መንግስት የሚያስፈልገን ለምን እንደሆነ ሲናገር፡-“በማህበር ከመሰባሰባቸው በፊት ተፈጥሯዊው የሰዎች ሁኔታ ጦርነት ነበር፤ ቀላል ጦርነት ሳይሆን ሁሉም ሰዎች ከሁሉም ሰዎች ጋር የተፋጠጡበት ጦርነት፡፡” መንግስት እንዲቀጣ መኖር አለበት የሚል ሃሳብ አለው፡፡ ይህ ደግሞ በዘመናችን ካለው legitimate -/position/ power ከሚለው ጋር የሚመሳሰል ይመስላል፡፡ ይህ ስልጣን ሌሎችን የመቆጣጠሪያ፣ የማስተዳደሪያ መሳሪያ ነው፡፡ ለምሳሌ እንደ መምህር፣ፖሊስ፣ወዘተ መንግስት መኖር ግድ ያለው የሰው አውሬያዊ ጠባይ ነው- እንደ ሆብስ አባባል፡፡ የዚህ ተቃራኒ ደግሞ ሄነሪ ዴቪድ ቶሩ የተባለው ፈላስፋና ጸሃፊ ነው፡፡ ቶሩ ፈጽሞ መንግስት መኖር የለበትም ነው የሚለው፡፡ ጥሩ የሚባል መንግስት የለም ባይ ነው፡፡ የሰዎችን ነጻነት ነጥቆ ህይወታችውን ይረብሸዋል ይላል፡፡…ይህ ሰው በነኤመርሰን ዘመን የነበረ የቅርብ ዘመን ሰው ነው፡፡ ዣን ዣክ ሩሶ ሌላው የመጽሃፉ እንግዳ ነው፡፡ ሩሶ የካልቪን እምነት ተከታይ(ፕሮቴስታንት) እንደ ነበረ ይገልጻል፡፡ ሩሶ በርግጥም የፕሮቴስታንትና የካቶሊክ እምነት ተከታይ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ አሁን በቀጥታ ቃል በቃል ባላስታውሰውም እምነቱን የተወበት ምክንያት ጥቅም ሳይሆን ፣ክርስትና ለነጻነት ትግል አያመችም በሚል እሳቤ ነው፡፡ ያ ብቻ አይደለም ፤ሩሶ ፈላስፋ ነው፣ወይስ አይደለም የሚሉ ሁለት ጎራዎችም አሉ፡፡..የሩሶን ጉዳይና ህይወት በሚያትተው ጽሁፉ ጸሃፊው ቃል ኪዳን ግልጽ ያላደረገልን ነገር ያለ ይመስለኛል፡፡
ምናልባት ልክ የሌለውንና ወደ ግብዝነት ያዘመመውን ጨዋነታችን(ትህትና) አስፈርቶት ይሆን?…እንዲህ የሚለው ነገር አልገባኝም፡-“…የሩሶ እናት ትዳር ከመመስረትዋ በፊት የፍቅር ግንኙነት መጀመሯ በሌላ በማንኛውም ቦታ ያንን ያህል ተጋንኖ ሊታይ የማይችል ጉዳይ ቢሆንም ጄኔቫ ውስጥ ግን ተሰምቶ የማይታወቅ ዓይነት ቅሌት ተደርጎ ተቆጥሯል፡፡” ምናልባት የግብረ ስጋ ግንኙነት ፈጽማ ነበር ለማለት ይሆን? የዚህ ዓይነቱ ነገር ቢነገር ምን ጣጣ አለው!...ምላስ ላይ ሳይሆን ተግባር ላይ መጠንቀቅ ይሻል ይመስለኛል፡፡ ንግግሩን ጠልቶ ነገሩ ላይ ከበረቱ በእግዜርም በሰውም ፊት ዋጋ የለውምና ህዝቡም ይህንን ቢለምድ ደስ ይለኛል፡፡ ራስን ማታለል አይጠቅምም፡፡ ያፈጠጠ ጸያፍ ካልሆነ ስንሸፋፍነው ሃሳቡን ያዛባልና ቃልኪዳን --- ግድ የለህም በለው፡፡ ወደ ማጠቃለያ ከመምጣቴ በፊት ፖለቲካዊ ትግልን ከሰላማዊ ትግል ጋር አጣምሮ የሚያስበውን ጋንዲን መጥቀስ የሚያስፈልግ ይመስለኛል፡፡ ጋንዲ ጆርጅ ዉድ ኩክ በጻፉለት የህይወት ታሪክ መጽሃፍ ውስጥ እንዲህ ተጠቅሷል፡፡…who did not fear to be violent, but chose deliberately to be non violent and to fight by power of truth rather than by the power of body. ይሁን እንጂ በዚህ ሰላማዊ ትግሉም እስርና ጉስቁልና አልቀረለትም፡፡ ቀደም ሲል የጠቀስኳቸው ደራሲ እንዲህ ይላሉ በመጽሃፋቸው፡-“Gandhi entered yeravda prison, near poona, with a great deal of composure. he is already familiar with the predictable routines of prison life,~ ሰዎች ይህንን እንደ ተጋነነ ቢቆጥሩትም ጋንዲ እስር ቤቱን እንደ እረፍት ስፍራ ይቆጥረው ነበር፡፡ በርግጥም ከላይ እንደ ተጠቀሰው እስር ቤት መግባት ለርሱ ተደደጋጋሚ የህይወት ጎዳና ነበር፡፡
በሰለጠነው ዓለምና በሰለጠነ ህዝብ መሃል ሰላማዊ ትግል በጣም የተለመደ እየሆነ መጥቷል፡፡ የዚህ ቀማሪና ጀማሪ ደግሞ መንግስት አያስፈልግም ባዩ ሄነሪ ዴቪድ ቶሩ ነው፡፡ ማርቲን ሉተር ኪንግም ይህንኑ ተከትሎ ውጤት አስገኝቶበታል፡፡ ምንም ቢሆን ሰላማዊ ትግል ከመገዳደል የሚሻል ይመስለኛል፡፡ ይህንን እንደ ማታለያ ወስደው የሚሸቅጡ መንግስታት ቢኖሩም አንድ ቀን ውጤት ሊያመጣ ይችላል ብሎ መቀበል የተሻለ ነው፡፡ ወደ ማጠቃለያ ስመጣ የ“ኢቦኒ” መጽሄት አዘጋጅ የሆነው ቃል ኪዳን ይበልጣል “ፖለቲካዊ ፍልስፍና” በሚል መጽሃፉ እጅግ በጣም ጥሩ ስራ እንደሰራ ሳልናገር አላልፍም፡፡ አንዳንድ ቦታ በጣም በአጋጣሚ ጥቂት ስህተት ከማየቴ ውጭ (ለምሳሌ ገጽ 44 ላይ ስለክርስቲያናዊ ፈላስፎች የሚያወራበት ቦታ ‹በአጭሩ ሰው ሀጥአን ነው፡፡ ብሏል፡፡ ሀጥዕ- መባል ሲገባው! በዚሁ ገጽ “የፖለቲካ ቲዮሪስትነቱ” የሚለው አልተመቸኝም፡፡ ምክንያቱም በአማርኛና በእንግሊዝኛ መሃል ተንጠልጥሏል፡፡ ካልሆነ ዶክተር ፈቃደ እንደሚለው “ትወራ” ቢለው ይሻላል፡፡ እርሱም የአማርኛ ቋንቋን የሚገድል አካሄድ በመሆኑ አይመችም፡፡ ከዚህ በቀር በቋንቋ አጠቃቀም፣በጽሁፉ ፍሰት፣በቅደም-ተከተላዊ ትረካው እጅግ የሚመስጥና የሚስብ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ለፖለቲከኞች ብቻ ሳይሆን ዕውቀት ለጠማቸው ሁሉ የሚያስጨብጠው ስንቅ አለ፡፡ እኔ ደስ ብሎኝ አንብቤዋለሁ፡፡ ውበትና እውቀትን አይቼበታለሁ፡፡ ቃልኪዳን ይበልጣል ተሰጥዖም ጥረትም አለህ በርታ - አሪፍ ነው!!

ከአዲስ  አድማስ ጋዜጣ የተወሰደ

Friday, May 3, 2013

አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን ታሰረች

“የፍርድ ሂደቱ ሲጠናቀቅ ጋዜጣዊ መግለጫ እንሠጣለን” - ከጀማነሽ ጋር የታሰሩ አባት
በተለያዩ የመድረክ ቴያትሮች፣ በቴሌቪዥንና በሬዲዮ ድራማዎች በተለይም “ገመና” በተሰኘው ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ የእናትነት ገፀ - ባህሪን ተላብሳ በመተወን የምትታወቀው አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን ታሰረች፡፡ አርቲስቷ ማክሰኞ ማታ ተይዛ አራት ኪሎ የሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ከታሰረች በኋላ ረቡዕ አመሻሽ ላይ ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ መዛወሯንና ከእርሷ ጋር ሌላ አንዲት ሴትና ሁለት ወንዶች መታሰራቸውን በስፍራው ተገኝተን አረጋግጠናል፡፡ አርቲስት ጀማነሽና አብረዋት የታሰሩት ግለሰቦች ሃሙስ እለት አፍንጮ በር መንገድ አዲስ አበባ ሬስቶራንት አካባቢ በሚገኝ የመጀመሪያ ደረጀ ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸው የታየ ሲሆን የፊታችን በድጋሚ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡
አርቲስቷንና አብረዋት የታሰሩትን ሰዎች ለመጠየቅ ወደ ስፍራው ከመጡ ግለሰቦች ለመረዳት እንደቻልነው፤ አርቲስቷና አብረዋት ያሉት ሰዎች የታሰሩት “ማህበረ ስላሴ ዘ ደቂቀ ኤልያስ” ከተባለው ማህበራቸውና ከሀይማኖት ጉዳይ ጋር በተያያዘ እንደሆነ ጠቁመው ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡ ከአርቲስቷ ጋር የታሰሩት አንድ የሃይማኖት አባት፤ ጉዳዩ በፍርድ ቤት የተያዘ በመሆኑ ከፍርድ ሂደቱ በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ፣ አሁን ምንም አይነት ዝርዝር መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ነግረውናል፡፡ አርቲስት ጀማነሽን ሊጠይቋት የመጡ ሰዎችን ለማነጋገር ስትወጣ በተመለከትናት ጊዜ በፈገግታ የታጀበች ሲሆን ጠያቂዎቿ “እንዴት ነሽ ተመቸሽ?” ብለው ሲጠይቋት “እግዚአብሔር ያለበት ቦታ ሁሉ ምቹ ነው” ስትል ምላሽ ሰጥታለች፡፡ አርቲስቷ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “ተዋህዶ” በሚል ሃይማኖት ውስጥ ተሣታፊ በመሆን አነጋጋሪ ሆና መቆየቷ የሚታወስ ነው፡፡
ወረዳ ዘጠኝ ፖሊስ ጣቢያ በተገኘን ጊዜ የሃይማኖቱ ተከታዮች የሚለብሱት የቀስተደመና ቀለማት ያሉት ነጠላ አጣፍታ፣ ፀጉሯንም የቀስተ ደመና ቀለም ዙሪያውን ባቀለመው ሻሽ አስራለች፡፡ ማህበረ ስላሴ ዘ ደቂቀ ኤልያስ “የኢትዮጵያን ትንሣኤ ሊያረጋግጥ ሃያል ባለስልጣን ነብዩ ኤልያስ ከብሔረ ህያዋን ጳጉሜ 1/2003 ዓ.ም ወደ ምድር መጥቶ በመካከላችን ይገኛል፣ ኦርቶዶክስ የሚባለው የሃይማኖት ስም ስህተት ነው ተዋህዶ ነው መባል ያለበት፣ ሰንበት ቅዳሜ ብቻ ነው፣ መለበስ ያለበት እግዚአብሔር ለኖህ ቃል ኪዳን የገባበትን ቀስተ ደመና ቀለማት ያካተተ ጥለት ያላቸው ነጭ አልባሳት ናቸው” የሚሉትን የተለያዩ ጉባኤዎችን እያዘጋጀ የሚያስተምር ማህበር መሆኑን ያነጋገርናቸው የማህበሩ አባላት ገልፀውልናል፡፡ በተለያዩ ገዳማትም የሀይማኖቱ አራማጆች እንደሚገኙና እንደሚያስተምሩ ያገኘናቸው የሃይማኖቱ ተከታዮች ነግረውናል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ከፖሊስ መረጃ ለማግኘት ጥረት ብናደርግም፣ ከመምሪያው የተፃፈ ፈቃድ ያስፈልጋል በሚል የወረዳው ፖሊስ መረጃ ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡

ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ የተወሰደ



ከአብርሽ ጋር ሲያዩኝ “ኮንግራ ሙሽራው ተገኘ?” ይሉኛል…




ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ የተወሰደ

 ከአብርሽ ጋር ሲያዩኝ “ኮንግራ ሙሽራው ተገኘ?” ይሉኛል…
ፈረንሳይ ትንሿ የኢትዮጵያ ሆሊዉድ ትባላለች…
የጠበሰም የተጠበሰም፤ የጠየቀም የተጠየቀም የለም (ስለትዳሯ)
በአዲስ አበባ ውስጥ ፈረንሳይ ለጋሲዮን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተወልዳ አድጋለች፡፡ ከልጅነቷ ጀምሮ ማንጐራጐር ይቀናት የነበረችው ትንሿ አበባ፤ እንጉርጉሮዋን በማሣደግ በቀበሌ ክበብ አድርጋ፣ በምሽት ክበብ አቋርጣ እስከ ትልቁ ብሄራዊ ቴአትር ቤት ጉዞዋን ቀጥላለች፡፡ ከድምፃዊነት በተጨማሪ በቴአትር መድረክም ላይ ችሎታዋን ያሣየችበትን “ልደት” ቴአትርና “አንድ ምሽት”ን ሠርታለች፡፡ ወደ ፊልሙም ሠፈር ጐራ ብላ “ሩሀማ” እና “ሠካራሙ ፖስታ” ላይ ተውናለች፡፡ ማስታወቂያውንም ሞክራለች፡፡ “ሙሽራዬ ቀረ” የሚል ተወዳጅ አልበም አውጥታ በጣም ተወዶላት ነበር፡፡ አርቲስቷ አምስት ዓመት ገደማ ድምጿን አጥፍታ ከቆየች በኋላ ሠሞኑን “የለሁበትም” የተሠኘ አዲስ አልበም ለማውጣት ደፋ ቀናውን ተያይዛዋለች፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛዋ ናፍቆት ዮሴፍ፤ ከአበባ ደሣለኝ ጋር በነበራት ቆይታ በአዲሱ ስራዋ፣ ጠፍታ ስለከረመችበት ጉዳይና ሌሎችንም የሥራና የህይወት ቁምነገሮች አንስታ ተጨዋውተዋል፡፡ እነሆ:-
የት ጠፍተሽ ከረምሽ?
ጠፋ ብያለሁ ግን ሥራ እየሠራሁ ስለነበር ነው፡፡ አሁን በአዲስ ስራ እየመጣሁ ነው፡፡ እስከዛሬ ቅጽል ሥም እንዳለሽ አልነገርሽንም? አንቺ ከየት ሰማሽ? እኔ ሰሞኑን ሰምቻለሁ፡፡ ከራስሽ እንስማው…
ማነው ቅጽል ስምሽ?
የሚገርመው ወደ ኪነ-ጥበብ ገብቼ ከ “እርጂኝ አብሮ አደጌ” እስካሁን ድረስ ብዙ ቃለ - ምልልስ አድርጌያለሁ፡፡ እኔም አልተናገርኩም፡፡ ሰዎችም ቅጽል ስም እንዳለኝ አያውቁም፡፡ ሰምቶም የጠየቀኝ የለም፤ አንቺ የመጀመሪያ ነሽ ስለ ቅጽል ስሜ ስትጠይቂኝ ማለቴ ነው፡፡ ስሜ “ሙናና” ነው የሚባለው፡፡ ይሄንን ስም ቤተሰቤ፣ እህቶቼ፣ የቅርብ ዘመድ እና የሠፈር ሰው ነው የሚያውቀው፡፡ ምን ማለት ነው? ስወለድ በጣም ቀጫጫና ትንሽ ነበርኩኝ አሉ፡፡ ካደግኩም በኋላ መወፈር አልቻልኩም፡፡ እና አሁን ይህቺ ሰው ሆና ታድጋለች… የሆነች ሙንን ያለች ነገር ብላ አያቴ ስትናገር፣ በዛው ሙናና ተባልኩኝ፡፡ አንዳንዶቹ ሙኒኒ ብለው ይጠሩኛል፤ ሰፈር ውስጥ ማለት ነው፡፡
እዚህ ለመድረስ ውጣውረዶችን እንዳሳለፍሽ ይነገራል፡፡ እስኪ አጫውቺኝ?
ከሌሎች ሰዎች በጣም የተለየ ውጣ ውረድ አይደለም ግን እንደማንኛውም ባለሙያ እዚህ ለመድረስ ከፍና ዝቅ ይኖራል፡፡ ምክንያቱም አንድ ነገር ሲጀመር ሁሉም አልጋ በአልጋ አይሆንም፤ በየትኛውም የስራ ዘርፍ ቢሆን ማለት ነው፡፡ ፈተናዎቹ እንግዲህ ከክበብ ጀምሮ እስከ ቴያትር ቤት፣ ከዚያም አልበም እስከማውጣት ደፋ ቀና ማለት ያለ ነው፡፡ ናይት ክለብ ስሰራም እንደዚሁ ሴትነትሽን ተከትለው ከሚመጡት ፈተናዎች ጀምሮ የተለያዩ ነገሮች አሉ፡፡ ዋናው ነገር እነሱን በድል ተወጥቼ እዚህ መድረሴ ነው፡፡ ይህ እንግዲህ እግዚአብሔርም ተጨምሮበት ነው፡፡ ከልጅነትሽ ጀምሮ ታንጐራጉሪ ነበር፡፡ በዛን ጊዜ የእነማንን ዘፈን ትዘፍኚ ነበር፡፡ የሂሩትን ዘፈኖች ለመጫወት የመረጥሽበትስ ምክንያት ምንድን ነው?
በነገርሽ ላይ ልጅ ሆኜ የወንድም የሴትም ዘፈን አይቀረኝም፡፡ ሁሉንም በቃ መዝፈን ነው፡፡ ለምሳሌ ደረጀ ደገፋውና ማርታ ሀይሉ እየተቀባበሉ የሚዘፍኑትን “አንቺ ሆዬ ሆይ” የተሰኘ ዘፈን፣ የሷንም የእሱንም ራሴን በራሴ እየተቀባበልኩ እዘፍን ነበር፡፡ ወንዱንም ሴቷንም እየሆንኩ ማለቴ ነው፡፡ የኬኔዲና የየሺመቤትን ዘፈን አሁንም ወንዱንም ሴቷንም ሆኜ እዘፍን ነበር፡፡ የጋሽ ጥላሁንንም እዘፍናለሁ፡፡ ያው ልጅ ስትሆኚ መምረጥ የለም፡፡ ሁሉንም መነካካት ነው፡፡ ከዚያ በኋላ መዝፈን ማለት ምን እንደሆነ፣ ሜጀር ማለት ምን ማለት እንደሆነ ሲገባሽ፣ መድረክ አያያዝ፣ ማይክ አጨባበጥ ምን እንደሆነ ስታውቂ፣ የማንን ዘፈን ብዘፍን ለድምፄ ከለር ይስማማል በሚል መምረጥ ትጀምሪያለሽ፡፡ እኔም ይሄ ሲገባኝ የፍቅር አዲስን፣ የብዙነሽ በቀለን፣ የሂሩትን፣ የማርታ ሀይሉን እና የሌሎችንም በመዝፈን ነው ወደራሴ የመጣሁት፡፡ የሂሩትን ዘፈን የዘፈንኩት የተለየ ምክንያት ኖሮኝ ሳይሆን ዘፈኖቹን በጣም ስለምወዳቸው ነው፡፡ ናይት ክለብ (የምሽት ክለብ) ውስጥ ረዘም ላለ ጊዜ እንደመስራትሽ ብዙ ገጠመኞችና ፈተናዎች ይኖሩሻል ብዬ አስባለሁ፡፡
እስኪ ከገጠመኞችሽ ጥቂት አውጊኝ? ናይት ክለብ ስሠራ የተለየ የገጠመኝ ነገር የለም፡፡
ግን አምሽቼ ስወጣ ቤቴ ሩቅ ስለነበር ለመሄድ እቸገር ነበር፡፡ የሚያደርሰኝ ሰርቪስ የለም፡፡ ፈረንሳይ ለጋሲዮን ድረስ መሄድ ለእኔ ትልቅ ፈተና ነበር፡፡ አንዳንዴ ጓደኛዬ ቤት ሳድር ቤተሰቤ ይጨነቃል፡፡ በግድ ነው እንጂ እንድሠራም አይፈቀድልኝም ነበር፡፡ ሌላው በወቅቱ ተማሪ ስለነበርኩኝ ደብተር ይዤ ናይት ክለብ የምሄድበት ጊዜ በርካታ ነበር፡፡ በተለይ ፈተና የደረሰ ሰሞን አንድ እዘፍንና እንደገና ደብተር ይዤ እቀመጣለሁ፡፡ በዚህ መልኩ ነው 12ኛ ክፍልን የጨረስኩት፡፡ ከዛ በተረፈ ናይት ክለብ ስትሠሪ የሚወድሽ ይኖራል ወይም የሚናደድብሽ ይኖራል፡፡ በርቺ አሪፍ ነው የሚልሽ ይኖራል፡፡ የሚያመናጭቅ ይኖራል፤ ይሄን ሁሉ አልፌያለሁ፤ የተለየ ገጠመኝ ግን የለኝም፡፡
ስለ ብሔራዊ ቴአትር ቤት ቆይታሽ እናውራ፡፡
ብሔራዊ ቴአትር ቤት ታሪካዊና ቀዳማዊ እንደመሆኑ እዛ በቋሚነት ለመቀጠር ብዙ እንደሚለፋ ሰምቻለሁ አንቺ እድሉን አግኝተሽ ለስምንት ወይም ለሰባት ዓመት ያህል ሰርተሽ እንደገና በራስሽ ፈቃድ መልቀቅሽን ነው የሰማሁት እንዴት ለቀቅሽ? እውነት ለመናገር ብሔራዊ ቴአትርን በጣም ነው የምወደው፡፡ ስገባም ፀልዬ ፈጣሪዬን ለምኜ እንደውም ተስዬ ብል ነው የሚቀለኝ፤ እንደዛ ነው የገባሁት፡፡ እንዳልሽው ብሔራዊ ቴአትር ቤት ትልቅ ቤት ነው፤ ብዙ ባለሙያዎችን ያፈራ ነው፤ አሁንም ብዙ ሙያተኞች አሉት፡፡ በዛን ሰዓት ከክበብ ተነስሽ በአንዴ ቴአትር ቤት መግባት ትልቅ ነገር ነው፡፡ ይሄ ከዛሬ ዘጠኝና አስር ዓመት በፊት ነው፡፡ እዛ በመስራቴ እና የታሪኬ አንድ አካል በመሆኑ ደስተኛ ነኝ፡፡ በወቅቱ 20 ሰው ተወዳደረ፤ የሚፈለገው ግን አንድ ሰው ነበር፡፡ ምንም እንኳ ማስታወቂያውን አይቼ መጀመሪያ ብመዘገብም የፈተናው ቀን ግን በጣም አረፈድኩኝ፡፡
በምን ምክንያት?
ባስ አጥቼ ሁሉም ሰው ተፈትኖ ካለቀ በኋላ ደረስኩኝ፡፡ ከዚያም ፈታኞቹን እባካችሁ ብዬ ለምኜ፣ እስኪ እንያት ተብሎ እድል ተሰጠኝ፤ ግን ፈጣሪ ተጨምሮበት ፈተናውን አልፌ ተቀጠርኩኝ ማለት ነው፡፡ በወቅቱ ስትቀጠሪ በድምፃዊነት ነበር፡፡ ከዚያ ቴአትርም ሰርተሻል፤ ኧረ ተወዛዋዥም ነበርሽ ነው የሚባለው፡፡ እውነት ነው?
ለመጀመሪያ ጊዜ የተጫወትሽውን ቴአትርም በዚያው ንገሪኝ …?
እርግጥ የተቀጠርኩት በድምፃዊነት ነው፡፡ ቴአትር ስሠራ አይተውኝም አያውቁም፡፡ ነገር ግን የቀበሌ ክበብ ውስጥ ቴአትር እሠራ ነበር፡፡ ሲራክ ታደሰ ያዘጋጀው “ልደት” የተሰኘ ትርጉም ቴአትር ነበር፡፡ በወቅቱ ካስት ሲያደርጉ “ይህቺ ልጅ ያቺን ገፀ ባህሪ ታመጣታለች” ብለው መረጡኝ፤ ስፈተንም አለፍኩኝ፤ እሱን ቴአትር ስጫወት ከእነ አርቲስት ጌታቸው ደባልቄ፣ ተስፋዬ ገ/ሀና፣ ትዕግስት ባዩ፣ ሱራፌል ወንድሙ ጋር ነበር፡፡ እነዚህ ትልልቅ አርቲስቶች ናቸው፡፡ በቴሌቪዥን አይቼ ከማደንቃቸው ጋር በአንዴ ተቀላቀልኩኝ፡፡ ቴአትሩ ለአንድ አመት ታይቷል፡፡ ከዛም በኋላ በደብል ካስት ልምምድ አደርግ ነበር፡፡ “ልደት” ቴአትር ላይ በጣም ተሳክቶልኛል፡፡ እንደነገርኩሽ በክበብ ደረጃ ድምጽም፣ ቴአትርም፣ ውዝዋዜም እሠራ ነበር፡፡ ውዝዋዜውን የተውኩት አጭር ስለሆንኩ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ “አንድ ምሽት” የሚል ቴአትር የጐዳና ሴተኛ አዳሪ ሆኜም ሰርቻለሁ፡፡ ትንሽ ክፍል ብትሆንም ስጫወት ጥሩ ነበርኩኝ፡፡ እንዲህ እንዲህ እያልኩ ነው የቆየሁት፡፡
ታዲያ እንዴት ቴአትር ቤቱን ለቀቅሽ?
እንደምታውቂው የሰው ልጅ አንድ ቦታ ላይ አይቆምም፡፡ ፍላጐት እየጨመረ ሲሄድ ነገ የተሻለ ነገር ማግኘት ይፈልጋል፡፡ እኔም የማደግ የመለወጥ ተስፋ ነበረኝ፡፡ እዚያው ቴአትር ቤት እያለሁ “እርጂኝ አብሮ አደጌ” የተሰኘው ከትዕግስት ፋንታሁን ጋር የሠራሁት አልበም ወጣ፡፡ ከዚያ በኋላ ለስራ ወደ ውጭ እፈለግ ጀመር፡፡ ፈቃድ ወስጄ ወጣ ብዬ ሠርቼ እመለስ ነበር፡፡ በመሀል ነጠላ ዜማም መስራት ጀመርኩኝ፡፡ በመጨረሻ “ሙሽራዬ ቀረ” አልበሜ ወጣ፡፡ በዚህ ጊዜ ከበፊቱ የበለጠ የውጭ ጥሪዎች መብዛት ጀመሩ፡፡ አንዴ አረብ አገር፣ አንዴ አውሮፓ ማለት ጀመርኩኝ፡፡ በመጨረሻ ግን አሜሪካ የተጠራሁበት ሥራ የስድስት ወር ስለነበር ፈቃድ አልሰጡኝም፡፡ እንደነገርኩሽ መለወጥ ማደግ ስለምፈልግ፣ ለስድስት ወር የምትሄጂ ከሆነ ትለቂያለሽ የሚል ነገር መጣ፤ እሺ ብዬ ሄድኩኝ ማስታወቂያ ተለጠፈብኝ፤ በዚህ ምክንያት ነው ቴአትር ቤቱን የለቀቅኩት፡፡ እንደሰማሁት ሰሞኑን ያንቺን ህይወት የሚዳስስ፣ ግለ ታሪክሽን የሚናገር ዘጋቢ ፊልም (ቪዲዮ) እያሠራሽ ነው፡፡ ስለሱ ጉዳይ ትንሽ ብታብራሪልኝ?
እዚህ አገር የተለመደው አንድ ሰው ሲሞት ታሪኩ ከዚህም ከዚያም ተለቃቅሞ ለአንድ ጊዜ ብቻ እከሌ በዚህ ጊዜ ይህን ሰራች (ሠራ)፣ የህይወት ዘመኑ ይህን ይመስላል ተብሎ በዚያው ይረሳል፡፡ ይሄ ከሚሆን አንድ ሰው በህይወት እያለ ትክክለኛ ግለ ታሪኩ የት ተወልዶ የት አደገ፣ የት ተማረ፣ በህፃንነቱ ምን አይነት ሰው ነበር፣ መልኩስ አስቀያሚ ነበር፣ ባህሪውስ? የሚለውን ኦውቶባዮግራፊ ቢያሰራ ጥሩ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ በአንድ በኩል ደግሞ ፕሮሞሽንም ነው፡፡ ምናልባት አበባን ሰው የሚያውቃት “እርጂኝ አብሮ አደጌ”ን ከሠራች በኋላ ሊሆን ይችላል፤ ከዚያ በፊት የነበራትን ነገር አያውቀውም፤ ምን አይነት ፈተናዎችን አልፋለች፣ አይናፋር ነበረች ወይስ በልጅነቷ ረባሽ ነበረች፣ በትምህርቷስ ውጤቷ ምን ይመስል ነበር፣ የሚሉትንና መሰል ጉዳዮችን ሰው ቢያውቀውና ከአሁኑ ማንነት ጋር ቢያስተያየው ደስ ይላል በሚል ቪዲዮውን እያሰራሁ ነው፡፡ አንቺ አሁን ገና ከወጣትነቱ አልወጣሽም፤ ከአንቺ ብዙ ስራዎች ይጠበቃሉ፤ የግለ ታሪኩ ስራ ትንሽ አልፈጠነም?
እንዳልሽው ብዙ ይጠበቃል፤ ያኔ አሁን በተሰራው ላይ እየተጨመረ ስለሚሄድ አሁንም ቢሠራ ችግር አለው ብዬ አላስብም፡፡ አሁን መሠራቱ እንደውም ወደፊት በእኔ መንገድ መጓዝ ለሚፈልግ ብዙ ትምህርት ይሆነዋል፡፡ በአንድ ነጠላ ዜማ ተነስቶ ታዋቂ መሆን እንደማይቻል፣ ብዙ ውጣ ውረድ እንዳለ፣ እንዴት መታለፍ እንደሚችል ይማሩባታል ብዬ አስባለሁ፡፡ በተረፈ ቅድም እንዳልኩሽ በልጅነቴ ያለው ነገሬ የሚያስቅም ነገር ይኖረዋል እና የሚያዝናና ይሆናል፡፡ ለምሣሌ የዱሮ ፎቶዬን ሲያዩ “እንዴ አባባ እንደዚህ አስቀያሚ ነበረች?” አሊያም “ወይኔ ስታምር” የሚሉ ይኖራሉ እና ሊያዝናና ይችላል ብዬ አስባለሁ፡፡
“እርጂኝ አብሮ አደጌ”ን ከዘመድሽ ከትዕግስት ፋንታሁን ጋር ሠርታችሁ ተወዶላችኋል፤ ከዚያ በኋላ አብራችሁ አላየናችሁም፡፡ ለምን ቆመ?
የሚገርምሽ የቆመ ነገር የለም፡፡ በእኔና በቲጂ መካከል ያለው ግንኙነት የቆመ ይመስላል እንጂ አልቆመም፡፡ እንሠራለን፣ በየቀኑ እንገናኛለን፣ በየጊዜው እንደዋወላለን፡፡ ነገር ግን የህይወት መንገድ አንዳንዴ አስቸጋሪ ነው፡፡ በተለይ ባለ ትዳር ስትሆኚ፣ ልጅ ስትወልጂና የቤተሠብ ሀላፊ ስትሆኚ ቤቴን ቤቴን ይመጣል፣ ወይ እኔ ተነስቼ ለስራ አንዱ አገር እሄዳለሁ፣ ቲጂም ተነስታ ወይ አሜሪካ ትሄዳለች፡፡ አየሽው አሁን የህይወት ጐዳና ወዲያና ወዲህ እንደሆነ፡፡ በዚህ ምክንያት እንደድሮው ተረጋግቶና ተጣምሮ ለመስራት ይከብዳል፡፡ ሩጫው አልገጣጠም ብሎን ነው ያልሠራነው፤ በሌላው ግንኙነታችን አብረን ነን፡፡ አሜሪካም በአንድ ወቅት አብረን ሠርተናል፡፡ ለምሣሌ የዛሬ ሁለት ዓመት አሜሪካ አንድ ቤት ነበርን፤ አብረን ሠርተናል፤ ቱር አብረን ነበር የምንወጣው እና ይሄን ይመስላል፡፡ “ሙሽራዬ ቀረ” የተሠኘውን ዘፈን ስትጫዎቺ ሙሽራዉ የእውነት የቀረ ያህል ስሜትን ጨምድዶ ይይዛል፡፡ ለዘፈን ብለሽ ሳይሆን የደረሠብሽ ነው የሚመስለው፡፡ ሙሽራ የቀረበት ዘመድ ወዳጅ አጋጥሞሻል ወይስ በቅርብ የምታውቂው ጉዳይ አለ?
የህዝቡስ ምላሽ ምን ይመስላል?
የሚገርምሽ ነገር “ሙሽራዬ ቀረ” በጣም ተፅዕኖ የፈጠረ ስራ ነው፡፡ አሁንም ድረስ ወይ ከአብርሽ ጋር (ባለቤቷ ነው) ሲያዩኝ ወይም የጋብቻ ቀለበቴን ሲያዩት “ኮንግራ ሙሽራው ተገኘ?” ይሉኛል፡፡ በእኔ ላይ ደርሶ የዘፈንኩት የሚመስላቸው አሉ፡፡ በአጋጣሚ ሀሣቡ መጣ፣ አብርሽ ፃፈው፤ ሮማን አየለ ዳይሬክት ስታደርገው የባሠ ነፍስ ዘራና እንዲህ አነጋጋሪ ዘፈን ሆነ፡፡ በጣም ተመስጬ የእውነት አስመስዬ የሠራሁት ቁጭ ብዬ ስሜቱን አስበው ስለነበር ነው፡፡ ይሄ ዘፈን በወጣ ሠሞን ብዙ ሙሽሮች ቀርተው፣ ድግስ አበላሽተው በ“ፖሊስና ህብረተሠብ” ፕሮግራም ላይ መመልከት ጀምረን ነበር እኮ፡፡ አጋጥሞሻል?
አጋጥሞኛል፤ አይቻለሁ፡፡ እኛ ባንሠማና ባናይ በየቦታው ይሄ ነገር ይከሠታል፡፡ እስኪ አስቢው የእኛን አገር ባህል? አንድ ሴት ተዘጋጅታ ድግስ ተደግሶ፣ ወዳጅ ዘመድ ተሠብስቦ፣ ሙሽራው ሲቀር ምን ያህል እንደሚያሸማቅቅ፡፡ በዘፈኑ እኔ መንገድ ስከፍት፣ ብዙ ሠው ሙሽራው እንደቀረ በክስ መልክ መናገርና ፖሊስም ለማስተማር በቴሌቪዥን ሲያሣየን ነበር፤ ብቻ ዘፈኑ የማንንም ቤት ሊያንኳኳ የሚችል፣ ያንኳኳባቸውንም ብሶት የቀሠቀሠ ስለሆነ በጣም ተወዶ ተደምጧል፡፡
ከሙዚቃና ቴአትር ባሻገር በ “ሩሃማ” እና “ሠካራሙ ፖስታ” ላይ በፊልም ትወና ብቅ ብለሽ ነበር፤ አሁን እልም ብለሻል፡፡ ማስታወቂያም ላይ ተመልክተንሻል፤ አሁን እሱም የለም፣ እንደገና በበጐ ፈቃድ አገልግሎት እንደምትሳተፊ ሠምቻለሁ? እስቲ በዚህ ዙሪያ አውጊኝ… ከፊልሙ እንነሣ፡፡ “ሩሀማ” ፊልም ላይ ያው ሩሃማን ሆኜ ተጫውቻለሁ፡፡ ፊልሙን አይተሽው ከሆነ ሩሀማ በጣም የምታሣዝን ሴተኛ አዳሪ የነበረች ከዚያ የህይወት ብርሀን ያየችና ያ ብርሀን መልሶ የጠፋባት ሴት ናት፤ ጥሩ ተሳክቶልኝ ሠርቼዋለሁ፡፡ እኔ እንደዚህ አይነት ገፀ-ባህሪ አይከብደኝም፡፡ ለምን ብትይ በተፈጥሮዬ አልቃሻና ሆደ ባሻ ነኝ፡፡ ፊቴም ለዚያ አይነት ባህሪ ምቹ ስለሆነ መሠለኝ እዛ ቦታ ላይ የሚመድቡኝ፡ ፊልሙን ትተሽ “እርጂኝ አብሮ አደጌ”ን አስቢው፤ እዛ ላይ ተጨንቄ ፊቴ እንደሚያሣዝን ነው የሚታየው፡፡ “ሠካራሙ ፖስታ ላይም እንዲሁ አሳዛኝ ሴት ሆኜ ነው የሠራሁት፡፡ ይህቺ ሴት ኤች አይቪ በደምሽ ውስጥ አለ ተብላ፣ ራሷን ከማህበረሠቡ ለማግለል ገዳም የምትገባ ግን ከገዳም የሚመልሣት ሠው ያገኘች ሴት ናት፡፡ ሁሉም ላይ እንዲህ አሣዛኝ ክፍል ላይ ነው የሚመርጡኝ፡፡ ማስታወቂያን በተመለከተ ብዙ ባልገፋም ሞክሬያለሁ፡፡ ሁለት ወይ ሶስት ማስታወቂያ ነው የሠራሁት፡፡ አንዱ በፊት ነው፤ አለሙ ገ/አብ ነፍሱን ይማረውና መርጦኝ፣ ጋሽ ውብሸት ወርቅአለማሁ ጋ ለእንቁጣጣሽ በዓል ከጓደኞቼ ጋር ስንዘፍን፣ እኔ ከጐጆ ቤት ወጥቼ ሠንደል ሳጨስ እታያለሁ፡፡ ከዚያ በኋላ ከሠራዊት ፍቅሬ ጋር አምባሣደር ልብስ ላይ ሠርቻለሁ፡፡ ብቻ ብዙ የሚወራለት አይደለም ማስታወቂያው፡፡ ፊልሙ አሁን ቆሟል፡፡ ብዙ ትኩረቴን ያደረግሁት አልበሙ ላይ ነው፡፡ በመሀልም ያው በስራ ምክንያት አሜሪካ ስድስት ወር እሠራለሁ፣ እመጣለሁ፡፡ እንደዚህ ሆነና ግጥም ዜማ ስሠበስብ በቃ ፊልሙ ተረሣ፤ ነገር ግን የመስራት ፍላጐት አለኝ፡፡ በጐ ፈቃደኝነትን በተመለከተ “እናት ለምን ትሙት” ዘመቻ ላይ “እችላለሁ” የሚል ዘፈን ሠርቻለሁ፡፡ ከሌሎችም አርቲስቶች ጋር የበጐ ፈቃድ ዘፈኖችን ሠርቻለሁ፡፡ ወደፊትም የበጐ ፈቃድ ሥራ የመስራት ፍላጐት አለኝ፡፡ አሁን በአልበሙ ስራ ሩጫ ላይ ስለሆንኩ እንጂ እቀጥላለሁ፡፡ በተለይ በትራፊክ ችግር፣ በእናቶች ሞት፣ በህፃናት መደፈርና በመሠል ማህበራዊ ችግሮች ላይ የመስራት ፍላጐት አለኝ፡፡ ከአልበሙ በኋላ እመለስበታለሁ፡፡ አሁን ወደ አዲሱ ሥራሽ እንምጣ በቅርቡ ከአሜሪካ የመጣሽው አዲስ አልበም ልታወጪ መሆኑን ሰምቻለሁ…
አዎ፡፡ አሜሪካ ስራ ላይ ነበርኩኝ፡፡ ከስራዬ ጐን ለጐን ለአልበሜ ግጥምና ዜማ እዛም ካሉ ባለሙያዎች ስሠበስብ ነበር፡፡ አሁን በጣም ጥሩ የሆነ የተለያየ ስብስብ፣ ባህልም ዘመናዊም፣ ጉራጊኛም ያካተተ ሥራ ሠርቻለሁ፡፡ ሠውም በጉጉት እንደሚጠብቅ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ የአልበምሽ መጠሪያ “የለሁበትም” ይሠኛል፡፡ ከምኑ ነው የሌለሽበት?
የለሁበትም እንግዲህ… አንቺ ከብዙ ነገር የለሁበትም ልትይ ትችያለሽ፤ ነገር ግን ይሄ ዘፈን የፍቅር ዘፈን ነው፡፡ ትክክለኛ ሀሣቡ በትዳር ወይም በጓደኝነት ብቻ በፍቅር ውስጥ ያለች ሴት ናት፡፡ ነገር ግን ባሏ ወይም ፍቅረኛዋ እሷን አይንከባከባትም፤ ጊዜ አይሠጣትም፤ ብቻ እንደ ፍቅረኛ ከጐኗ አይሆንም፡፡ የእሷን ድካም ፍቅር አይረዳም፤ ስለዚህ “እባክህ ከእኔ ጋር ከሆንክ አብረን ፍቅራችንን እናጠንክር፤ እምቢ ብለህ እኔ ሀሣቤን ብቀይር በኋላ የለሁበትም” በሚል ነው የምታስጠነቅቀው፡፡
አልበምሽ በዋናነት በምን ላይ ያተኩራል?
ሁሉንም ያካትታል፡፡ ቀደም ብዬ እንደነገርኩሽ ከከተማ እስከ ገጠር የሚዳስስ ነው፡፡ አሁን ስለ ገጠሩ ህይወት የሚዳስስ “ባጥ አሣቅሉኝ” (ጐጆ አቃልሱኝ) እንደማለት ነው፡፡ አይነት ደስ የሚል ዘፈን ሁሉ አለው፡፡ ይህ ዘፈን የአገሬው ሠው ሆ ብሎ ቤት እንዲያሳራት የምትማጠንበት ነው፡፡ ሁለት የሂሩት ዘፈኖች ተካተውበታል፣ “ተረት ተረት”፣ “ቸር ወሬ” የሚሉና ሌሎችም ምርጥ ምርጥ ዘፈኖች ተካተዋል፡፡ በአጠቃላይ 13 ያህል ዘፈኖች አሉት፡፡ አዲስ ሥራ ሲሠራ እነማን ተሳተፉ የሚል የተለመደ ጥያቄ አለ፡፡ አንባቢም ስለሚጠብቅ በግጥም፣ በዜማ፣ በቅንብር ማን ማን እንደተሳተፈ ንገሪኝ? ጌራወርቅ ነቃጥበብ፣ ተመስገን አፈወርቅ፣ አስቻለው ዲሮ በዜማ ተሣትፈዋል አብርሽም በግጥም ተሣትፏል፤ ሁለት ዜማም አለው፡፡ ሄኖክ ነጋሽ የሁለት ባህላዊ ዘፈኖች ዜማ ሠጥቶኛል፡፡ ደሣለኝ መርሻ የተሳተፈበት ጉራጊኛ አለኝ፡፡ የሂሩትን ሁለቱን ስሠራ አንዱ ላይ አርቲስት ተስፋዬ አበበ (ፋዘር) በግጥም ተሣትፎበታል፤ ሻምበል መኮንንም ተሣትፎ አድርጐበታል፡፡ ሌሎች ባለሙያዎች ተሣትፈዋል፡፡ ሌሎች ባለሙያዎችም ተሣትፈዋል፡፡ ቅንብሩስ…? ካሙዙ ካሣ አራት ዘፈኖችን፣ አስቻለው ዲሮ ሶስት፣ ሄኖክ ነጋሽ አንድ ዘፈን፣ እያሱ እስራኤል አለ፤ ተሾመ ጥላሁን፣ አሸብር ማሞ እና ኢዮብ ፋንታሁን ያቀናበሩት ሲሆን ሚክሲንጉን አስቻለው ዲሮ ሠርቶታል፡፡ በአጠቃላይ ብዙ ደክሜበታለሁ፡፡ ወጪውም ወገቤን የሚያሠኝ ነው፡፡ ከወጪው ባሻገር ከተለያየ ባለሙያ ጋር ሲሠራ ብዙ ስሜቶችን አስተናግዶ፣ ታግሶ ማለፍ አስፈላጊ በመሆኑ ፈታኝ ነበር፡፡ አሜሪካ ሲሄድ ስመጣ ብቻ ወደ ሁለት ዓመት ፈጅቷል፡፡ ገንዘቡ፣ ጉልበት፣ የሠዎች ትብብር ሳይጨመር እንኳን ከባድ ነው፡፡ አሁንም ወጪ ላይ ስለሆንኩ ይሄን ያህል አውጥቼአለሁ ልልሽ ግን አልችልም፡፡ የማሣትመውም ራሴ ነኝ፡፡ ኮከብ ሙዚቃ ቤት ለማከፋፈል ስምምነት አለን፡፡
መቼ እንጠብቅ?
እኛ እግዜር ከፈቀደ ለፋሲካ ብለናል፡፡ በሩጫ ላይ ነን፡፡ እንግዲህ ማስተሪንግ የምናሠራባቸው ህንዶች ሠሞኑን ሲዲ አልቆብናል ብለውናል፤ ግን አሁን እናስመጣለን ብለዋል፡፡ እሱ ካለቀልን ለፋሲካ አሪፍ ስራ እናበረክታለን፡፡ ለአንዳንዶቹም ዘፈኖች ክሊፕ እየሠራሁ ነው፡፡ ከስራሽ ወጣ እንበልና ስለ አንቺና ስለ ባለቤትሽ አብርሀም (አብርሽ ዘጌት) ትንሽ እናውራ ይቻላል፡፡ በፊት ጥሩ ወንድምና እህት ሆናችሁ፤ ረጅም ጊዜ ቆይታችሁ በሠዎች ወሬ ባልና ሚስት ሆናችሁ ይባላል፡፡ እንደውም “ወሬውን ሠምቻለሁ” የተባለው ነጠላ ዜማሽ የተዘፈነው ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ነው ይባላል፡፡ ምን ያህል እውነት ነው? እንዳልሽው እኔ እና አብሪ ግንኙነታችን ክለብ ውስጥ ነው፡፡ እኔም ልዘፍን እሱም ሊዘፍን መጥቶ ማለት ነው፡፡ የሚገርምሽ ግን ሁለታችንም የፈረንሳይ ልጆች ሆነን ግን አንተዋወቅም ነበር፡፡ እሱ የአቦ ሠፈር ልጅ ነው፤ እኔ 07 ቀበሌ ነኝ ግን አንተዋወቅም፡፡ ካዛንቺስ “አልማዝ ላሊበላ” የተባለ ክለብ ነው የተገናኘነው፡፡ ከዚያ ሌሎች ቤቶችም አብረን በመስራት በወንድምነትና እህትነት ረጅም የጓደኝነት ጉዞ አድርገናል፡፡
ግን የሆነ ሠዓት ላይ ዝም ብለን ትዳር አደረግነው እና ህይወት ቀጠለ፡፡ የጠበሠም የተጠበሠም የለም እያልሽኝ ነው? (ሣ…ቅ) አዎ የጠበሰም የተጠበሠም፣ የጠየቀም የተጠየቀም የለም፡፡ እኛ ከፍቅር ግንኙነት ውጭ በጣም ጓደኛሞች ሆነን ስንኖር ሠዎች ዝም ብለው ያወሩ ነበር፡፡ ይሄም አንድ ምክንያት ነበር፡፡ እንዳልሽው “ወሬውን ሠምቻለሁ አሜን ይሁን ብያለሁ” የተሠኘው ነጠላ ዜማም ከዚሁ ጋር ግንኙነት አለው፡፡ ሠርግም ግርግርም የለም፤ ከዚያ ክርስቲያን አብርሀም ተወለደች፤ እሷው አጋባችን፡፡ አሁን አምስት አመት ሞላት፡፡ ለክርስቲያን ወንድምና እህት አልሠጣችኋትም? አዎ ገና አልመጣም፡፡ ምክንያቱም ሩጫው ትኩረት እንድንሠጥ አላደረገንም እና አላሠብንበትም፡፡ ተወልደሽ ያደግሽው እውቁ አትሌት ዋቢ ቢራቱ ሠፈር በመሆኑ ሯጭ ትሆኛለች ተብሎ ሲጠበቅ አንቺ ዘፋኝ ሆነሽ አረፍሽው… በመሠረቱ ከፈረንሳይ ብዙ ጥበበኞች ወጥተዋል፡፡ ሁሌ “ከውሀው ነው መሠለኝ” እንላለን፡፡ ትንሿ የኢትዮጵያ ሆሊውድም ትባላለች፡፡ ከያኒ፣ ጋዜጠኛ፣ ሯጭ ብቻ ጥበበኞች አሏት ፈረንሳይ፡፡ እኔ እንደ ዋሚ ቢራቱ ሯጭ ባልሆንም ዘፋኝ ሆኛለሁ ለማለት ነው፡፡ በመጨረሻ ከ “የለሁበትም” አልበምሽ ምን ትጠብቂያለሽ? እኔ ጥሩ ነገር እጠብቃለሁ፡፡ ሁሉንም ያማከለ ስራ ነውና፡፡ ወጣቱም ጐልማሣውም ሊያዳምጠው የሚችለው ስራ ነው፡፡ ከእኔ ጋር ብዙ የደከሙ ባለሙያዎች፣ ጓደኞች፣ ባለቤቴ አብርሽ በጣም ሊመሠገኑ ይገባል፡፡ ቢጂ አይ ኢትዮጵያንም አመሠግናለሁ፡፡ እና አሪፍ ነገር አለ ብዬ ነው የምጠብቀው፡፡ “አንቺ የለሁበትም” እንዳልሽው፣ አልበምሽን አሪፍ አድርገሽ ባታመጪ “እኛም የለንበትም”… አብረን የምናየው ይሆናል፡፡ በጣም አመሠግናለሁ ሙናና፡፡ እኔም ከልብ አመሠግናለሁ፡፡

Wednesday, May 1, 2013

የጊቢ ሞት በተባለ ኦፕሬሽን በየመን ወደ 1000 የሚጠጉ ኢትዮጵያዊያን ከአፋኞች ነጻ ወጡ

የጊቢ ሞት በተባለ ኦፕሬሽን በየመን ወደ 1000 የሚጠጉ ኢትዮጵያዊያን ከአፋኞች ነጻ ወጡ
                                                       ግሩም ተ/ሀይማኖት
     ለሰሞኑ የየመንን መገናኛ ብዙሃን ትኩረት የሳበው የኢትዮጵያያኑ ላይ እየጠፈጸመ  ያለው አሰቃቂ ስራ ሲሆን ከችግሩ ጀርባ ያለውን እውነታንም በይፋ እየተናገሩ ነው፡፡ እስከዛሬ የነበረ ድምጻችን፣ መፍትሄ ይፈለግ ጥያቄያችን ሰሚ አግኝቶ የየመን መንግስት በየቦታው ያሉ ታጋቾችን ሲያስለቅቅ ከችግሩ መፈጠር ጀምሮ እስከ መንግስት አካላት ድረስ መነካካት እንዳለበት አጋልጠዋል፡፡ አሁንም ከአጋቾቹ ነጻ ከወጡ በኋላ ስደተኞቹ ላይ አግባብ ያልሆነ ነገር እየተፈጸመ እንደሆነ ዘግበዋል፡፡ ስለሁኔታውና የዘገቡትን እውነት እያመሳከርኩ እንይ፡-
      ባለፈው ረቡዕ ምሽት ማታ ተንቀሳቃሽ ስልኬ ደጋግሞ ‹‹ወሬ ሊያቀብልህ የመጣ ሰው አለ ክፈት..ክፈት..›› እያለ አንቃጨለ፡፡ ቁጥሩን የማወቀው ወዳጄ እና የሞያ አጋሬ ጋዜጠኛ መሀመድ ደርማን ነው፡፡ መሀመድ ደርማን ኢትዮጵያዊያኑ በህገ-ወጥ አጓጓዦች እየታገቱ የሚደርስባቸው ስቃይ የውስጥ እግር እሳት ሆኖ ያቃጥለዋል፡፡ እውነታውን ከመረጃ ጋር ካሳየሁት በኋላ በቁጭት እሳት ተርመጥምጦ ከሞት ጋር ለመታገል ቆርጦ ተነሳ፡፡ ይሄ ሰብዓዊነት የተላበሰ ሀሳቡ ነው ያገናኘን፡፡ ያግበባን፡፡ ከዚህ በፊት በሁለት ዙር የየመን መንግስት ወታደሮች ከአጋቾቹ ጋር ተዋግተው ኢትዮጵያዊያኖቹን ነጻ ሲያወጡ ቦታው ላይ በመገኘት ዘግቧል፡፡ ባለፈው ሳምንት ግን የመንግስት አካላት እጅ እንዳለበት ከዘገበ በኋላ ችግር ተፈጠረ፡፡ ደጋግሞ የሚያንጫርረው ስልኬን ከፈትኩት…
   ‹‹አሎ! ኬፍ አለክ ያ-አኪ ጉሮም አነ መሀመድ ደርማን…›› እንደምነህ ወንድሜ ግሩም እኔ መሀመድ ደርማን ነኝ የሚለውን ቃሉን አቀበለኝ፡፡ ‹‹አረፍት ኬፈክ ያ-ሪጃል ሰሀፊ!››  አውቄሀለሁ አንተ ወንድ(ጎበዝ) ጋዜጠኛ አልኩት
    ‹‹አልዬም  ሾዬ መርቡሽ አሸን ከወፉኒ ሙጅሪሚን…›› ዛሬ ትንሽ ተረብሻለሁ፡፡ አሸባሪዎቹ ረበሹኝ አለኝ እና ነገ እንገናኝ የሚለውን አስከተለ፡፡ በማግስቱ በተቀጣጠርንበት ሰዓት ቤቴ መጣ፡፡ የተረበሸው ቢሯቸው ፎቅ ስር 400 ግራም የሚመዝን ቲንቲ /TNT/ ፈንጂ አጥምደውባቸው ሳይፈነዳ ለደህንነቶች ጠቁመው መክሸፉን ነገረኝ፡፡
      ቀጣይ በዚህ ጉዳይ ላይ የበለጠ እንዲሰራ አደረጉት እንጂ ፈርቶ ወደኋላ እንደማይል ነገረኝ፡፡ ያበርታህ የሚለውን በሆዴ አልጎመጎምኩ፡፡ ይህን ያነሳሁት አፋኞቹ ምን ያህል የጠነከሩ ሲነኳቸው ለማጥፍት እንደሚሄዱ ላሳየት ነው፡፡ አጠቃላይ ዘገባውን ስቃኝ ደግሞ…በዚህ ወር ብቻ ባህሩን ተሻግረው የመን ከገቡ ኢትዮጵያዊያኖች መካከል በአጋቾች ከተያዙት ውስጥ ወደ 1000 የሚሆኑት ነጻ ወጡ፡፡ በሀረጥ ዙሪያ ካሉ አካባቢዎች ድንበሩን ጠባቂዎች እና የመንግስት ወታደሮች(የመከላከያን ሰራዊት) በማስተባበር አካባቢውን በመፈተሸ ከአንድ ጊቢ ብቻ 210 አስፈቱ፡፡ በ22/04/13 እሁድ ዕለት ከተያዙት ውስጥ 89 ሴቶች ሲሆኑ 10 ህጻናት ናቸው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኛዎቹ በግርፋት፣ በድብደባ፣ በእሳት ማቃጠል፣ በመደፈር..የተጎዱ አካላቸው የደቀቀ እና የተጎሳቆሉ ናቸው፡፡
      ከአፈና የተፈቱት የሰጡትን ቃል ስንመለከት……ካህሳይ ሚኬሌ እና ወንድሙ የደረሰባቸው ግፍ በጣም ሰቅጣጭ ነው፡፡ ‹‹..በጣም በጣም ነው የደበደቡን፡፡ በብረት ሁሉ ደብድበውናል፡፡ ላስቲኩን በእሳት እያቃጠሉ ሰውነታችን ላይ ያንጠባጥቡታል፡፡ ስልክ ሰተውህ ለዘመዶችህ ደውል ይሉሀል፡፡ ደውለህ የሚልክልህ ከሌለ ዘመዶችህ እንዲሰሙ ነው እላይህ ላይ የቀለጠውን ላስቲክ ጠብ እያደረጉ ስትቃጠል እና ስትጮህ ቤተሰቦችህ እንዲወሰሙ ያደርጋሉ፡፡ በዚህ ስቃይ መካከል ወንድሜ ህይወቱ አለፈ፡፡ገንዘብ ለማግኘት ወጥተን ወንድሜን በሞት አጥቼ ሌሎቻችንም አካላችንን ከፈልን..›› በማለት ተናግሯል፡፡ ለስምንት ወርም በእንግልት ቆይቷል፡፡
    ንጉሴ በግሩፕ ሲጓዙ ከነበሩት አንዱ ነው፡፡ ‹‹.ከባህር እንደወረድኩ ተያዝኩ፡፡ ተደበደብኩም፡፡ ከሚደበድቡት መካከል ኢትዮጵያዊያንም አሉበት፡፡ ከድብደባ ብዛት ግራ እግሬ ተሰበረ፡፡ ስቃዩ ሲብስብኝ ወደ ኢትዮጵያ ደወልኩ፡፡ ግዳቸውን የሳዑዲ 1000 ሪያል ላኩልኝ፡፡ ተደብድቤ አካሌ ከጎደለ በኋላም ቢሆን ተላከልኝ አውጥተው በረሃ ላይ ጣሉኝ፡፡ ሲጥሉኝ ራሴን አላውቅም ነበር፡፡ ስነቃ ራሴን ጭው ያለ በረሀ ስጥ አገኘሁት፡፡ደግ የመናዊያን አግኝቼ 10 ኪሎ ሜትር ወስደው ተከምኩኝ፡፡ ይህን ድርጊት የሚፈጽሙት ሀይል ያላቸው እና ከመንግስት ሰው ያላቸው ናቸው፡፡….›› ንጉሴ ከኢትዮጵያ ላኩልኝ ብሏል፡፡ በደንብ ስላላብራራው እኔ ልግለጸው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ ወኪላቸው በፖሊስ ተይዞ ፍርድ ካገኘ በኋላ ዘዴ ቀይረዋል፡፡ ሳዑዲ አረቢያ የሚያውቁት ሰው ይፈልጉ እና እሱ በሳዑዲ ሪያል 1000 ለእነሱ ይልካል፡፡ የታጋቹ ቤተሰቦች የሳዑዲ 1000 ሪያል የሚሆነውን በኢትዮጵያ ብር ከሳዑዲ ለላከላቸው ቤተሰቦች ይሰጣሉ፡፡
   አካባቢው ላይ ያለ ባለስልጣን ሲናገር ደግሞ ‹‹..ሆስፒታል ውስጥ 27 ሬሳ ፍሪጅ ውስጥ በስብሷል፡፡ የእነዚህ ሰዎች አሟሟ ት በስቃይ ለመሆኑ በሰውነታቸው ላይ ያለው ምልክት ያስረዳል፡፡ እስካሁንም ሬሳው ፍሪጅ ውስጥ ነው፡፡ መቅበር አልቻልንም፡፡ ፍርድ ቤቱ እንዲቀበሩ ቢፈርድም እስካሁን ከሶስት ወር በላይ ሆኗለወ አልተቀበረም፡፡ይህ የሆነው ግን መውበሪያ ስላጣን ነው፡፡አለም አቀፉ የስደተኞች ጽ/ቤት IOM እና UNHCR አንድ ላይ መሬት ሊገዙ ተስማሙ፡፡ እኛ ሁኔታውን ለማወቅ ከሆስፒታሉ ጋር መረጃ እንለዋወጥ ነበር፡፡ የሚገዛ መሬቱ ተገኘ አልተገኘ እንጠይቃለን፡ በኋላ መሬቱ ተገኘ ተስማሙ እና ተገዛ፡ በሳምንቱ ለመቅበር በቦታው ተገኘን፡፡ የሆስፒታሉ ሰራተኞች አምጥተው ሊቀብሩ ሲሉ የአካባቢው ሰው አይቻልም እዚህ አይቀበሩም አሉ፡፡ዳግም ሆስፒታል ተወስደው እ ነው አሁንም ሬሳው….›› ብሏል ባለስልጣኑ፡፡ ጋዜጠኛው ራሱ ሲመሰክር ‹‹..ማዳ የተባለ ቦታ ብዙ የስደተኞች ሬሳ አገኘን፡፡ የብዙዎችን ሬሳ በየበረሃው አገኘን፡፡ አሰቃይተው በእሳት ካቃጠሉዋቸው በኋላ ይጥሏቸዋል፡፡
  ይህን በተመለከተ አል-ተውራ ተብሎ የሚጠራው የመንግስት ጋዜጣ ደግሞ አካባቢው ላይ ያሉ ጉዳዩ የሚመለከታቸው በለስልጣናት በዝምታ መለጎማቸው እና መንግስት የሰጠው ክፍተት ለዚህ አንዳደረሰ ዘግቧል፡፡ በዘገባውም ሀረጥ አል-ዘሀራ የተባለ ቦታ 48 የታፈኑ ሰዎች አሉ፡፡ በተደጋጋሚ የመንግስት ወታደሮች ሊያስለቅቋቸው ሞክረው እነዚህን አጋቾች ሊረቱ ስላልቻሉ 48 ሰዎች እስካሁን እንደያዙዋቸው ነው፡፡ የመንግስት ወታደሮች ሲናገሩ አጋቾቹ ሊያስጠጉን አልቻሉም ስለዚህ ምን ማድረግ እንዳልብን አለወቅንም ብለዋል፡፡
    ይህ የሀገሪቱ ከፍተኛ የመንግስት ጋዜጣ የሚባለው ቶውራ የመንግስት ቁጥጥር መላላት እንደሆነ ለችግሩ መንስኤ ገልጾዋል፡፡ ይህ ወንጀል በሚሰራበት አካባቢው ያሉት የወታደር እና ደህንነት ዝም ማለት የፈለጉት አፋኞቹ (ህገ-ወጥ አጓጓዦቹ) ከጀርባቸው ትላልቅ የመንግስት ባለስልጣናት ስላሉ መሆኑን ዘግቧል፡፡    
       እኔ እስካውቀው ደግሞ ይ ብቻ አይመስለኝም፡፡ አይደለምም፡፡ አካባቢው ላይ ላሉ ባለስልጣናት ብቻ ሳይሆን ድንበር ጥበቃ ላይ ያሉት ሰዎች በባህር በገባው ስደተኛ ልክ ማለት በአንድ ሰው ሂሳብ እንዳላቸው የሚታወቅ ነው፡፡ እንዲያውም ከዚህ በፊት ባናገርኳቸው ሰዎች መረጃ መሰረት ጀልባው ቀድሞ ሲመጣ እንኳን ደውለው እንደሚጠሯቸው ነው፡፡ የመን ግልጽ ሙስና የሚከናወንባቸው ከሚባሉት ሀገሮች ተርታ በመሆኗ ሲታሰሩ እንኳን በገንዘብ ሀይል እንደሚወጡ የታየ እውነታ ነው፡፡ ማጣራት እስክችል ድረስ ስሙን ለመጥቀስ ባልፈልግም አንድ በዚህ ስራ የተሰማራ ኢትዮጵያዊ አግቶ ከያዛቸው 60 ኢትዮጵያዊያን ወገኖቹ ጋር የየመን መንግስት በቁጥጥር ስር አዋለው፡፡ ከ80000 የሳዑዲያ ሪያል ከፍሎ ከእስር ተፈታ፡፡ ይሄ ያለውን ሙስና ለማሳየት ያሰፈርኩት ይሁን እንጂ ኤምባሲውም ሊፋረደው ሲገባ በአቅራቢያው ያሉ እዛው ብቅ ጥልቅ የሚሉ ሰዎች ሲያስፈቱት ዝም ማለቱ ምን እንደሚያሳይ መገመት አያቅትም፡፡
      በኤምባሲ ዙሪያ ካነሳሁ በነካ አፌ ልጨርሰው እና ልለፍ፡፡ ሰሞኑን ቅጥ ያጣውን እና በየእስር ቤት ውስጥ ተሰግስጎ ያለውን ኢትትዮጵያዊያ ስደተኞች ወደ ሀገር ለማስገባት አለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት IOM የሚያደርገውን ጥረት በማገዝ ደፋ ቀና እያሉ መሆኑን ከቢሮው አካባቢ የገኘሁት መረጃ ያስረዳል፡፡ በየእስር ቤቱ ያሉትን ወደ 3000 ኢትዮጵያዊያን ወደ ሀገር ለማሰገባት የሚደረገውን ጥረት ተቀብለው አሁን በቅርቡም 469 ስደተኞችን ወደ ሀገር ለመመለስ መመለሻ ወረቀት (ሊሴ ፓሴ) እያጋጁ መሆኑም ታውቋል፡፡ ኤምባሲው አሁን ከምን ጊዜውም በላይ ትብብር ማሳየቱ ደስ የሚል ጅምር ነው፡፡  
     ወደ ጋዜጣው ገባ ስገባ በየቦታው የኢትዮጵያዊያኑ ሬሳ ወድቆ እንደሚገኝ፣ እንደሚታይ እና ጸሀሪው ራሱ በተወሰኑ ቦታዎች ላይ ማየቱን ተናግሯል፡፡ የቀሩትን ታጋቾች ለምን እንደማያስለቅቁ ሲጠይቃቸው አለመቻላቸው እና ከመንግስት ወታደር የተሻለ ሀይል እንዳለው እንደሚናገሩ ገልጾዋል፡፡ እንዲያውም በቦታው ላይ ያሉትን ሀላፊዎች ሲያናግራቸው ከፍርሃት የተነሳ አንድም ቃል አልሰጡንም፡፡ ለነፍሳቸው ፈሩ..ብሏል፡፡ አለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት IOM ጊቢ ውስጥ ሲገቡ ያዩት በጣም ሰቅጣጭ እንደነበረ የገለጸው ጋዜጠኛ ብረት አግለው ሰውነታቸውን ከጠበሷቸው አንስቶ አሰፈሪ እና ሰቅጣጭ ሁኔታ የተፈጸመባቸው ለማየት በቅተዋል፡፡ የድርጅቱ ሰራተኞች ግን በአስጸያፊ ስድብ በፖሊስ ከጊቢ እንዳስወጧቸው ዘግቧል፡፡ እንዲያውም እንዳንገባ እና ጉዱን እንዳናይ ዱላ ቀረሽ በሆነ ሁኔታ መለሱን፡፡
   ይህ ሁኔታ ሲታይ እነዚህ አለም አቀፍ ድርጅቶች ጉዱን እየደበቁ ተደፋፍኖ እንዲቀር የሚፈልጉበት ሁኔተሰ እንዳለ የዘገበ ሌላ ጋዜጠኛም አለ፡፡ እመለስበታለሁ፡፡