ስደት እና ፍቅር
በግሩም ተ/ሀይማኖት
ርዕሴን ሲያዩ ምን አገናኝቶት ስደትን ከፍቅር ጋር ለጠፈው እንዳይሉ፡፡ እመነኝ..እመኝኝ ግጥም አድረጎ ይገናኛል፡፡ ካላመንከኝ እንወራረድ ብዬ እንዳልሞግትህ ፍቅርን እንደ ፊልም የሚያሳይ ስክሪን የለኝም፡፡ መሞከሪያ ቴስት ላይትም አልተሰራለት…ወደፊት ከተሰራ አብረን እናያለን፡፡
የሰዎችን የፍቅር ታሪክ እንደመስማት የሚያስደስት ነገር አለ? ታዲያ ዝም ብሎ ፍቅር ብለው በየቤርጎው በየእንትኑ ስር የሚፈጽሙትን የአንቀህ ጣለኝ ድራማ አይደለም፡፡ የእውነተኛውን ፍቅር ታሪክ መስማት ያስደስተኛል፡፡ የእናንተን እንጃ ግን ባትውዱ ሁሉ ስለፍቅር የሚያወሩ እነዛን ሁሉ ጋዜጦች ተሸምታችሁ
በግሩም ተ/ሀይማኖት
ርዕሴን ሲያዩ ምን አገናኝቶት ስደትን ከፍቅር ጋር ለጠፈው እንዳይሉ፡፡ እመነኝ..እመኝኝ ግጥም አድረጎ ይገናኛል፡፡ ካላመንከኝ እንወራረድ ብዬ እንዳልሞግትህ ፍቅርን እንደ ፊልም የሚያሳይ ስክሪን የለኝም፡፡ መሞከሪያ ቴስት ላይትም አልተሰራለት…ወደፊት ከተሰራ አብረን እናያለን፡፡
የሰዎችን የፍቅር ታሪክ እንደመስማት የሚያስደስት ነገር አለ? ታዲያ ዝም ብሎ ፍቅር ብለው በየቤርጎው በየእንትኑ ስር የሚፈጽሙትን የአንቀህ ጣለኝ ድራማ አይደለም፡፡ የእውነተኛውን ፍቅር ታሪክ መስማት ያስደስተኛል፡፡ የእናንተን እንጃ ግን ባትውዱ ሁሉ ስለፍቅር የሚያወሩ እነዛን ሁሉ ጋዜጦች ተሸምታችሁ
ትገዙ ነበር፡፡ ለነገሩ አስትሮሎጂ የሚል ጥንቆላም አላቸው እሱንም ፈልጋችሁ ይሆናል፡፡ ስለ ፍቅር ማንበብ መስማት ቢያስደስትስ ምን ያሳፍራል? የሰውን ፍቅር የማይወድ ሴጣን ብቻ ነው፡፡
ስለምወድም የብዙዎችን የፍቅር ታሪክን ከሰማሁ በኋላ ነው ስደትና ፍቅር ብዬ የተነሳሁት፡፡ ውይ የኔ ነገር ተነሳሁ እንዴ? አረ!! አልተነሳሁም፡፡ ብዕሬን ያነሳሁት ለማለት ነው፡፡ ለካ ብዕርም አላነሳሁም ቀጥታ ሀሳቤን ወደ ኮምፒዩተር የተየብኩት በሚል ይቀየርልኝ፡፡ እንዲያውም አንዳንዴ ሳስብ ፍቅር ይሰደዳል አይሰደድም? የሚል መጠይቅ ቢቀርብ ስንት አይነት መልስ ይሰማል? ይሰደዳልም በሉ አይሰደድም ለጊዜው አቆዩኝ እና ‹‹ስደት ላይ ፍቅር ይከሰታል አይከሰትም?›› በሚል ርዕስ ውይይት ከሰዎች ጋር አነሳለሁ፡፡ ያላቸውን ሀሳብ ለማወቅ ግዴታ ተቃራኒ ሆኜ መቅረብ ይጠበቅብኛል፡፡ ‹‹ስደት ላይ ፍቅር አይከሰትም..›› ብዬ የውሸቴን ሽንጤን ገትሬ እከራከራለሁ፡፡ እንዲያው ለአባባል ሽንጤን ገትሬ አልኩ እንጂ እንኳን ልገትረው ለራሱ መኖር እና አለመኖሩን አይቼ አላውቅም፡፡ የት ጋር ይሆን ያለው? አሳዩኝ ምሩኝ መንገዱን…የሚለውን ዜማ ማቀንቀን ይጠበቅብኛል መሰለኝ ቦታውን ለማዎቅ፡፡ ለነገሩ ሽንጥ ያለው ስጋ ቤት ነው፡፡ እናላችሁ ስለፍቅር እናውራ….
ስከራከር አዎ! ካልኳቸው በዛው ተስማምተን እንዳንቀር እሰጋለሁ፡፡ ስለዚሀ ተቃራኒ እሆንና ተናደው የሚሰማቸውን እንዲያወሩ አደርጋለሁ፡፡ ይከሰታል ባይ መሆኔ ዝም ብሎ ሳይሆን እኔ ለራሴ ቤተ-ሙከራ ራሴ ነኝ፡፡ የሰው ልጅ ባለበት ሁሉ ፍቅር አለ ባይ ነኝ፡፡ ግን የትኛው የፍቅር አይነት የሚለው ነው መሰረታዊ ጥያቄ፡፡ ሰም ለበስ ፍቅር መስሎ የሸመቀውን፣ ፍቅር የሚለውን ታፔላ ለጥፎ ለጥቅም ሸምቆ የሚገኘውን አይደለም፡፡ ጥቅምን ታርጌት ያደረገውን የውሸት ፍቅር ፍጽሞ ከግምት አንከተውም፡፡ የምንነጋገረው ስለ እውነተኛው ፍቅር ነውና፡፡ እውነተኛው ፍቅርስ ቢሆን በስንት ይከፈላል? አንዳንዶች እንደ ሸንኮራ አገዳ ሰነጣጥቀው ሸንሽነው ሸንሽነው ያበዙታል፡፡ ለእኔ ግን ፍራንሲስ ቦምና ‹‹ፍቅር ውሻን እንኳን በዜማ እንዲያላዝን ያደርገዋል..›› እንዳለው ሀያል እና አንድ ብቻ መሆኑን ነው የሚገባኝ፡፡ አብሮኝም የተሰደደው እውነተኛው ፍቅር ነበር፡፡እንዲያውም አድንቄዋለሁ አብሮኝ በመውጣቱ…ብዕርም አስነስቶኛል፡፡
‹‹..ስደት ከሄድኩበት ነጻነት ፍለጋ
ፍቅርሽን ይዤ ከትዝታ ስዋጋ
ሀይል የለኝ ጉልበት
ታግዬ የማሸንፍበት…›› አስብሎኛል፡፡ በሰፊው ከከተብኩት ቦጨቅ ደረኩት ነው፡፡
አፈር ነህና ወደ አፈር ትመለሳለህ የሚለው ቃል ተግባራዊ ሆኖ አፈር እስካልተጫነው…አፈር ረገጠ ድንጋይ፣ ጎጆ ቀለሰ፣ ፎቆ ቆለለ ጎዳና አደረ፣ ስደት ወጣ እስር ቤት ገባ…ቦታና ጊዜ ሳይመርጥ አጅሬ ፍቅር ቂብ ይልበታል፡፡ ሌላው ቀርቶ ወዳጄ ሙት ለካ ሆድህ ባዶ ሆኖም ፍቅር አለ፡፡ ስደት ላይ ያገኘሁት ዋሲሁን…ውይ የኔ ነገር ጋሼ ዋሲሁን ማለት ነበረብኝ የሀያ አንድ አመት ልጅ አለችው እኮ!..ለነገሩ ራሱ ተመለጠ እንጂ አንድ ፍሬ ቦርቆ ያልጠገበ የሀምሳ ሰባት አመት ጎልማሳ ነው፡፡
ስማኝማ ዋሲሁን መቼም እኛ ‹‹ከአሜሪካና ከሞት የሚቀር የለም ካልን ሰነበትን ዛሬ አሜሪካ ሆነህ ነው የምታነበኝ እና የማታፍር ከሆነ የወሎ የፍቅር ታሪክህን ላስፍራት? አጭ!...ምን ሆንክ ግሩሜ ወደ ታሪክህ ተመለስ ያንተን ዋሲሁን እኛ የት እናውቅልሀለን….ብዬ ራሴን ተቆጣሁትና ተመለስኩ፡፡ ሆድ እርቦት የፍቅር ርሃብም ተደርቦ እንደሚያስቃይ የነገረኝ ዋሲሁንን ገጠመኝ እንመልከት፡፡ ‹‹በ1977 ወሎ በርሃብ ተጠቅቶ ነው፡፡ የሚላስ የሚቀመስ ታጥቶ ርሀብ ሲያሳድደን እኔን ግን እህል ብቻ ሳይሆን ፍቅርም እየራበኝ እሰቃይ ነበር፡፡ ወደ አሰብ ለመሄድ የተነሱ ቤተሰቦች በአካባቢያችን ሲያቋርጡ አይኔን ብቻ ሳይሆን በርሃብ የተጣበቀ አንጀቴን ጭምር አጠገበችው፡፡ በልቶ ሳይሆን እሷን አይቶ…እነሱ ሁለት ቀን አድረው ጎዞዋቸውን ቀጠሉ፡፡ ርሃብ ካደቀቀው እኔነቴ ላይ ልቤን መንትፋ ነጎደች፡፡ ታዲያ ያችው እምንቃመሳት እህል እንኳን አልበላ አለችኝ፡፡ ርሃቤ ጸሀይ ይመር ሆነች፡፡ ቤተሰቦቼን ይዤ ወደ አዲስ አበባ ልሄድ የነበረውን ሰርዤ እነሱንም ትቼ ወደ አሰብ አቀናሁ፡፡ ይሄው እስካሁንም ከቤተሰቦቼ አልተገናኘሁ፡፡ ታዲያ አላጣኋትም፡፡ የያኔዋ ጸሀይ ይመር የአሁኗ ባለቤቴ ሀያት ይመር ናት አንድ ልጅም ያስታቀፈችኝ እሷ ናት ብሎኛል፡፡ ከፈቀደ እጅግ ደስ የሚል ታሪኩን ሙሉውን አስነብባችኋለሁ፡፡
ለዋሲሁን ፍቅር ይሰደዳል ሳይሆን ፍቅር ያሰድዳል የሚለውም ይሰራል፡፡ ቤተሰቦቹን በዛ ችግር ወቅት አስትቶ አሰብ ያሰደደው ፍቅር ነው፡፡ ለእኔ የሚመስለኝ ሰው እስከተሰደደ ፍቅር የማይሰደድበት ምንም ምክንያት የለውም፡፡ ፍቅር ይሰደዳል የሚለውን ለማጠናከር ብዙ መዳከር የለብንም ብዙዎች ስንሰደድ ፍቅረኛ አልነበረንም? ከነበረንስ ፍቅራችንን እንደልብስ አውልቀን ጥለነው ወጣን? እኔ የራሴን የማስታውሰው የውዴን ፍቅር ሰንቄ ነበር ስደትን የተጋተርኩት፡፡ ስለዚህ ፍቅር ይሰደዳል፣ ፍቅር ያሰድዳል፣ ፍቅር ስደት ላይ ይከሰታል እላለሁ፡፡ እናንተስ? ለጊዜው በዚህ እንወያይ
በቀጣይ እመለሳለሁ፡፡
ስለምወድም የብዙዎችን የፍቅር ታሪክን ከሰማሁ በኋላ ነው ስደትና ፍቅር ብዬ የተነሳሁት፡፡ ውይ የኔ ነገር ተነሳሁ እንዴ? አረ!! አልተነሳሁም፡፡ ብዕሬን ያነሳሁት ለማለት ነው፡፡ ለካ ብዕርም አላነሳሁም ቀጥታ ሀሳቤን ወደ ኮምፒዩተር የተየብኩት በሚል ይቀየርልኝ፡፡ እንዲያውም አንዳንዴ ሳስብ ፍቅር ይሰደዳል አይሰደድም? የሚል መጠይቅ ቢቀርብ ስንት አይነት መልስ ይሰማል? ይሰደዳልም በሉ አይሰደድም ለጊዜው አቆዩኝ እና ‹‹ስደት ላይ ፍቅር ይከሰታል አይከሰትም?›› በሚል ርዕስ ውይይት ከሰዎች ጋር አነሳለሁ፡፡ ያላቸውን ሀሳብ ለማወቅ ግዴታ ተቃራኒ ሆኜ መቅረብ ይጠበቅብኛል፡፡ ‹‹ስደት ላይ ፍቅር አይከሰትም..›› ብዬ የውሸቴን ሽንጤን ገትሬ እከራከራለሁ፡፡ እንዲያው ለአባባል ሽንጤን ገትሬ አልኩ እንጂ እንኳን ልገትረው ለራሱ መኖር እና አለመኖሩን አይቼ አላውቅም፡፡ የት ጋር ይሆን ያለው? አሳዩኝ ምሩኝ መንገዱን…የሚለውን ዜማ ማቀንቀን ይጠበቅብኛል መሰለኝ ቦታውን ለማዎቅ፡፡ ለነገሩ ሽንጥ ያለው ስጋ ቤት ነው፡፡ እናላችሁ ስለፍቅር እናውራ….
ስከራከር አዎ! ካልኳቸው በዛው ተስማምተን እንዳንቀር እሰጋለሁ፡፡ ስለዚሀ ተቃራኒ እሆንና ተናደው የሚሰማቸውን እንዲያወሩ አደርጋለሁ፡፡ ይከሰታል ባይ መሆኔ ዝም ብሎ ሳይሆን እኔ ለራሴ ቤተ-ሙከራ ራሴ ነኝ፡፡ የሰው ልጅ ባለበት ሁሉ ፍቅር አለ ባይ ነኝ፡፡ ግን የትኛው የፍቅር አይነት የሚለው ነው መሰረታዊ ጥያቄ፡፡ ሰም ለበስ ፍቅር መስሎ የሸመቀውን፣ ፍቅር የሚለውን ታፔላ ለጥፎ ለጥቅም ሸምቆ የሚገኘውን አይደለም፡፡ ጥቅምን ታርጌት ያደረገውን የውሸት ፍቅር ፍጽሞ ከግምት አንከተውም፡፡ የምንነጋገረው ስለ እውነተኛው ፍቅር ነውና፡፡ እውነተኛው ፍቅርስ ቢሆን በስንት ይከፈላል? አንዳንዶች እንደ ሸንኮራ አገዳ ሰነጣጥቀው ሸንሽነው ሸንሽነው ያበዙታል፡፡ ለእኔ ግን ፍራንሲስ ቦምና ‹‹ፍቅር ውሻን እንኳን በዜማ እንዲያላዝን ያደርገዋል..›› እንዳለው ሀያል እና አንድ ብቻ መሆኑን ነው የሚገባኝ፡፡ አብሮኝም የተሰደደው እውነተኛው ፍቅር ነበር፡፡እንዲያውም አድንቄዋለሁ አብሮኝ በመውጣቱ…ብዕርም አስነስቶኛል፡፡
‹‹..ስደት ከሄድኩበት ነጻነት ፍለጋ
ፍቅርሽን ይዤ ከትዝታ ስዋጋ
ሀይል የለኝ ጉልበት
ታግዬ የማሸንፍበት…›› አስብሎኛል፡፡ በሰፊው ከከተብኩት ቦጨቅ ደረኩት ነው፡፡
አፈር ነህና ወደ አፈር ትመለሳለህ የሚለው ቃል ተግባራዊ ሆኖ አፈር እስካልተጫነው…አፈር ረገጠ ድንጋይ፣ ጎጆ ቀለሰ፣ ፎቆ ቆለለ ጎዳና አደረ፣ ስደት ወጣ እስር ቤት ገባ…ቦታና ጊዜ ሳይመርጥ አጅሬ ፍቅር ቂብ ይልበታል፡፡ ሌላው ቀርቶ ወዳጄ ሙት ለካ ሆድህ ባዶ ሆኖም ፍቅር አለ፡፡ ስደት ላይ ያገኘሁት ዋሲሁን…ውይ የኔ ነገር ጋሼ ዋሲሁን ማለት ነበረብኝ የሀያ አንድ አመት ልጅ አለችው እኮ!..ለነገሩ ራሱ ተመለጠ እንጂ አንድ ፍሬ ቦርቆ ያልጠገበ የሀምሳ ሰባት አመት ጎልማሳ ነው፡፡
ስማኝማ ዋሲሁን መቼም እኛ ‹‹ከአሜሪካና ከሞት የሚቀር የለም ካልን ሰነበትን ዛሬ አሜሪካ ሆነህ ነው የምታነበኝ እና የማታፍር ከሆነ የወሎ የፍቅር ታሪክህን ላስፍራት? አጭ!...ምን ሆንክ ግሩሜ ወደ ታሪክህ ተመለስ ያንተን ዋሲሁን እኛ የት እናውቅልሀለን….ብዬ ራሴን ተቆጣሁትና ተመለስኩ፡፡ ሆድ እርቦት የፍቅር ርሃብም ተደርቦ እንደሚያስቃይ የነገረኝ ዋሲሁንን ገጠመኝ እንመልከት፡፡ ‹‹በ1977 ወሎ በርሃብ ተጠቅቶ ነው፡፡ የሚላስ የሚቀመስ ታጥቶ ርሀብ ሲያሳድደን እኔን ግን እህል ብቻ ሳይሆን ፍቅርም እየራበኝ እሰቃይ ነበር፡፡ ወደ አሰብ ለመሄድ የተነሱ ቤተሰቦች በአካባቢያችን ሲያቋርጡ አይኔን ብቻ ሳይሆን በርሃብ የተጣበቀ አንጀቴን ጭምር አጠገበችው፡፡ በልቶ ሳይሆን እሷን አይቶ…እነሱ ሁለት ቀን አድረው ጎዞዋቸውን ቀጠሉ፡፡ ርሃብ ካደቀቀው እኔነቴ ላይ ልቤን መንትፋ ነጎደች፡፡ ታዲያ ያችው እምንቃመሳት እህል እንኳን አልበላ አለችኝ፡፡ ርሃቤ ጸሀይ ይመር ሆነች፡፡ ቤተሰቦቼን ይዤ ወደ አዲስ አበባ ልሄድ የነበረውን ሰርዤ እነሱንም ትቼ ወደ አሰብ አቀናሁ፡፡ ይሄው እስካሁንም ከቤተሰቦቼ አልተገናኘሁ፡፡ ታዲያ አላጣኋትም፡፡ የያኔዋ ጸሀይ ይመር የአሁኗ ባለቤቴ ሀያት ይመር ናት አንድ ልጅም ያስታቀፈችኝ እሷ ናት ብሎኛል፡፡ ከፈቀደ እጅግ ደስ የሚል ታሪኩን ሙሉውን አስነብባችኋለሁ፡፡
ለዋሲሁን ፍቅር ይሰደዳል ሳይሆን ፍቅር ያሰድዳል የሚለውም ይሰራል፡፡ ቤተሰቦቹን በዛ ችግር ወቅት አስትቶ አሰብ ያሰደደው ፍቅር ነው፡፡ ለእኔ የሚመስለኝ ሰው እስከተሰደደ ፍቅር የማይሰደድበት ምንም ምክንያት የለውም፡፡ ፍቅር ይሰደዳል የሚለውን ለማጠናከር ብዙ መዳከር የለብንም ብዙዎች ስንሰደድ ፍቅረኛ አልነበረንም? ከነበረንስ ፍቅራችንን እንደልብስ አውልቀን ጥለነው ወጣን? እኔ የራሴን የማስታውሰው የውዴን ፍቅር ሰንቄ ነበር ስደትን የተጋተርኩት፡፡ ስለዚህ ፍቅር ይሰደዳል፣ ፍቅር ያሰድዳል፣ ፍቅር ስደት ላይ ይከሰታል እላለሁ፡፡ እናንተስ? ለጊዜው በዚህ እንወያይ
በቀጣይ እመለሳለሁ፡፡
0 Comments:
Post a Comment
Subscribe to Post Comments [Atom]
<< Home