Saturday, November 10, 2012

የጅማ ልጆች ከድር ሰተቴን የምታስታውሱ…


የጅማ ልጆች ከድር ሰተቴን የምታስታውሱ…
                         በግሩም ተ/ሀይማኖት
      ጅማ ብዙ የሚወጉ ወጋ ወጎች አሏት፡፡ ብዕራቸውን ከአፎቱ የመዘዙ የጅማ ልጆች ይህችን ውበታም የፍቅር ከተማ መዳሰስ እና ማስዳሰስ አልቻሉም፡፡ በአንድ ወቅት ስሄድ መሀል ከተማ ላይ ለከተማዋ የውበት እንብርት ሆኖ የተኮፈሰው አዊቱ መናፈሻ መጸዳጃ ሆኖ ነበር፡፡ እህቴና እኔ አፍንጫችንን አፍነን ዞረን አየን፡፡ እንደ እህያ ጋማ አዊቱን ሁለት ቦታ ከፍሎ የሚያልፈው ወንዝ ደም ግባት እና ውበት ሆናት ሳለ ቦታው ማደሪያና መጸዳጃ መሆኑ አሳዛኝ እንደሆነ ጋዜጣዬ ላይ ጻፍኩ፡፡ ጅማ የሚጻፍ ብዙ ነገር አላት፡፡ የግድ ጅማን ከአባ ጂፋር ጋር ማቆራኘት የለብንም፡፡ አባ ጅፍርን ከጅማ ነው ማቆራኘት ቢያስፈልግ እንኳን፡፡

    ምንክንያት አንድ፡- አባ ጅፋር ሳይኖሩ ጅማ ነበርች አሁንም አለች፡፡
    
    ምንክንያት ሁለት፡- የጅማ ማህጸን አባ ጅፋርን ብቻ ሳይሆን ብዙዎችን አብቅሎዋል፡፡

    ምክንያት ሶስት፡- ዙሪያ ተፈጥዋን ስንቃኝ.. ቦዬ ራሱን የቻለ ምስጢር ነው፡፡ አዊቱ እንዲሁ.. ሰርቦ፣ በዳቡና..ሰዎችን እንይ ካልን /ደጃዝማች ይሁኑ ፊት አውራሪ ማዕረጋቸውን ረሳሁት../ አቶ ተካ ኤገኖ፣ ጋሽ ደርጉ…ከድር ሰተቴ..ብዙ የሚዳሰስ አለ፡፡ ለዛሬ አንዱን ጀመርኩ፡፡

     መውጫው ይሁን መግቢያው ሲጠፋቸው አንዳንዴ እብድ እየመሰሉ የልባቸውን የሚናገሩበት አጋጣሚ ሞልቷል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ከድር ሰተቴ ነው፡፡ ከድር የአባቱ ስም አይደለም ሰተቴ ‹‹ሰተተተትትትትት…›› እያለ የሴቶችን እንትን ሳያስቡት መንካት ይወዳል፡፡ እብድ ለመምሰል ብሎ ብቻ ሳይሆን ሳስበው እዛ ስር የተለከፈም ይመስለኛል፡፡ ቀርከሀ ዱላ ይይዛል፡፡ ጆኒዎከርም ይሉታል፡፡ እብድ መስሎ እብድ ያልሆነ ሁሌም ጽዱ ሆኖ የሚታይ፡፡ በሰከንዶች ውስጥ ግጥም እየገጠመ አጥረግርጎ ሚሳደብ ሲያሻው የሚያሞግስ፡፡ ለነገሩ አሞግሶ የሚያውቀው ኢህአፓን ብቻ ነው፡፡ በኢህአፓ የመጣበትን አይቀበልም፡፡ ቀንደኛ የኢህአፓ አባልና ታጋይ ነበር ሲባል ሰምተናል፡፡ ግን አላየንም፡፡ በ1977 ዓ.ም ወሎ ብድርቅ ተጠቅቶ ሰው በርሃብ እያለቀ አስረኛው የአብዬት በዓል ይከበር ነበር፡፡ ኢሠፓአኮም ወደ ኢሠፓ ይሸጋገር ነበር፡፡ ይሄ ጉዞ እድገት ይሁን ውድቀት ብዙ ፖለቲከኞች ግራ ሲጋቡበት እንጂ ሲተነትኑት አይስተዋልም፡፡ ምስጢሩን ጓድ መንግስቱ ብቻ ሳይሆኑ አልቀሩም የሚያውቁት፡፡ የሆነው ሆኖ ኢሠፓአኮ የሚለውን ‹‹ኢሳያስ ሰናይትን ፓንቷን አስወልቆ ኮሞኮማት›› ሲሉ በሰዓቱ ወጣቶቹ ያላግጡበት እንደነበር ትዝታ መጨለፍ እንችላለን፡፡

      ከድር ሰተቴ የሰባሰባቱን 10ኛ የአብዮት በዓል በተጋነነ ወጪ መከበር ከርሃቡ ጋር ሲገልጸው ‹‹ሰባሰባት አንድ እንጀራ ለሰባት…ሰባሰባት..አንድ እንጅራ ለሰባት….ኢሠፓኮ ባዶ ፓኮ›› ይል ነበር፡፡ በአንድ ወቅት የቀበሌ ፕሬዘዳንቶች…የመከላከያ ሚኒስትሮች… ማለቴ የቀበሌ ሊቀመንበሮች አብዮት ጠባቂዎች ራሳቸውን እንደ ፕሬዘዳንት እና መከላከያ ሚኒስቴር ስለሚመለከቱ በፍላጎታቸው ልጥራቸው ብዬ ነው፡፡ እዛችው ጅማችን ውስጥ ተሰብስበው አለም ደርግ ብለው ይጠጣሉ፡፡  ባዶ እጁን ሆኖ ሽጉጥ እንደያዘ በሽጎጥ ቅርጽ እጁን አድርጎ ‹‹እንዳትበላሽ እጅ ወደላይ..›› ይላል፡፡ ግማሾቹ ስተው ሁሉ ነበር አሉ፡፡ ቤቱን የፈነዳ ሽንት ቤት አስመስለውት፡፡ ተደናብረው የብርጭቆ መዓት የከሰከሱትን ቤት ይቁጠራቸው፡፡ ወይ ልባቸው!!! ከድር ሰተቴ ተያዘና ታሰረ፡፡ ‹‹እኛ ያልነው ለፉገራ እናንተ አደረጋችሁት የመግደል ሙከራ..›› ብሎዋቸው ነበር ይባላል፡፡  ስለከድር ሰተቴ ብዙ ማለት እችላለሁ፡፡ እስኪ እናንተ የምታስታውሱት ምን ያህሉን ነው?
   
       ስለ ጅማ እመለሳለሁ አዊቱ ሻይ እየጠጣችሁ ጠብቁኝ

1 Comments:

At November 10, 2012 at 9:09 AM , Blogger ግሩም ዜና said...

sile jimma yemawiqew kanbebikutna kesemahut selhon bizum yemawiqew yelegnm tariku temecitognal be mawiqew lay tinsh cemiriyalehu tnks

 

Post a Comment

Subscribe to Post Comments [Atom]

<< Home